ይህ ታሪክ ከተፈፀመ እነሆ በዛሬዉ 122ኛ ዓመቱን ይዟል። ይህ ቀን ለአሁኗ ኢትዮጵያ ማንነቷን ያስጠበቀችበት፣ ከባርነት ራሷን ነፃ ያደረገችበት ቀን ነው። ከመላው የአለም ኃያላን የተነሳን ከባድ የባርነት በትር በፅኑ ትግል ከጫንቃዋ ያነሳች ብሎም ለመላው የአፍሪካ ሀገራትና ህዝቦች የነፃነት ምክንያት ነበረች።
ታዋቂው አሜሪካዊ የወንጌል ሰባኪ ዊልያም ፍራንክሊን ግራሃም ወይም በአጭሩ ቢሊ ግራሃም በ99 አመታቸው ዜና እረፍታቸው በትላንትናው ዕለት (የካቲት 14) ማለዳ ከሳውዝ ካሮሊና ግዛት ከመኖርያ ቤታቸው ተሰምቷል። ይህ መረጃ እንደወጣ ሁለት ወዳጆቼ በሰአታት ልዩነት ደውለው ሲነግሩኝ እጅግ ነበር ያዘንኩት። ደግሞ በአካል አገኛቸው ዘንድ ምኞቴ እንደነበር ወዳጆቼ ስናገር ሰምተውኛል። እኔ በግሌ ከጽሁፍ ለጥቂት ወራት ርቄ የነበረ ቢሆንም የእርሳቸውን ሞት ስሰማ ግን ዝም ማለት አልሆነልኝም።
ከአድካሚ የስራ ቀን በኋላ ወደ ጊዜያዊ ማረፊያዬ እየሔድኩ ሳለሁ በውስጤ ብዙ ሃሳብ ይመላለስ ነበር። ተስፋ የላቸውም ብዬ የምቆጥራቸው ነገሮች ሲበዙ ከፈረሰው ነገር ባሻገር ማየት አቃተኝና ጥልቅ የሆነ ሃዘን ዉስጥ ገባሁ። ተስፋዬም እያሽቆለቆለ ሲሄድ ድምፅ አልባ በሆነ መቃተት ወደ እግዚአብሔር ተማፀንኩ።
አጥብቃችሁ በፈለጋችሁት ጊዜ ልታገኙት የምትችሉት የተስፋ መጠን እጅግ ድንቅ ነው። ተስፋ ደግሞ በሕይወታችን እጅግ አስፈላጊ የሆነ ኃይል ነው። ከእግዚአብሔር የመጨረሻ አሸናፊነት ወደ እኛ የሚፈስስ የደስታ ወንዝ ነው። "የእግዚአብሔር ደስታ ደግሞ ኃይላችን ነው" (ነህምያ 8፡10)። አይደለም በእግዚአብሔር ነገር ልንለመልም ይቅርና ያለተስፋ መኖር አንችልም።
ወደ እግዚአብሔር በቀረብንበት በዚያ ስፍራ ከመገኘቱ ጋር ደግሞ እንገናኛለን። በተዘረጉ እጆቹ ሊቀበለን ተዘጋጅቶ እናገኘዋለን። መገኘቱ ሊሰማን እንደሚገባ ከተሰማን በቅድስናው ታላቅነት ልንሸፈን እንችላለን። ይህን ደግሞ ኢሳይያስ ከእግዚአብሔር ጋር ሲገናኝ ከሆነው ማየት እንችላለን።
እንደምን አላችሁ?
ጥፋተኛ ብሆንም እነዚህ ቃላት እንደ ጥያቄ ሳይሆን እንደ ሠላምታ ሲቀርቡልኝ ትንሽ ይረብሸኛል። ተጨባጭ መልስ ሳንፈልግ “እንዴት ናችሁ?” ብሎ መጠየቅ ቀላል ነገር። አንዳንድ ጊዜ ሰዎች ከእርምጃቸው እንኳን ሳያቋርጡ ደህና ነህ? ብለውኝ ያልፋሉ። በእነዚህ ጊዜያት ብቸኛው ተገቢ መልስ “ደህና ነኝ” ነው የሚሆነው ምንም እንኳን ነገሮች ላይሆኑ ቢችሉም። የዚህ አይነቱ ጥልቅ ያልሆነ ሰላምታ ብዙውን የየዕለት መስተጋብራችንን ይሸፍናል። ግንኙነቶቻችንን ብዙ ጊዜ ከላይ ከላይ እንፈጽማለን ነገር ግን ወደ ልባችን ስላለበት ትክክለኛ ሁኔታ ጠልቀን አንገባም።
“ስለ በደላችን አልፎ የተሰጠውን እኛን ስለ ማጽደቅም የተነሣውን ጌታንችንን ኢየሱስን ከሙታን ባስነሣው ለምናምን ለእኛ ይቈጠርልን ዘንድ አለው።” ሮሜ 4፡24-25
በአላት በደረሱ ቁጥር በሄድንበት ቦታ ሁሉ የምናገኛቸው ሰዎች ደስተኞች መሆን እንዳለብን ይነግሩናል።
ይሁን እንጂ ወዳጆቻቸውን በቅርቡ ላጡ ሰዎች በዓሉ ሊደሰቱበት የሚገባቸው ነገር መሆኑ ቀርቶ እስኪያልፍ የሚጓጉት ነገር ሊሆንባቸው ይችላል። ለበአሉ ታላቅ ደስታን እና ትርጉምን መስጠት የሚችሉት ባህሎች እና ትዕይንቶች፣ የምንወደው ሰው ይህን ደስታ አብሮን ይካፈል ዘንድ አለመቻሉን በሚያስታውሱ አስጨናቂ ትውስታዎች ይዋጣሉ። ብዙዎች እነዚህ የበአል ወቅቶች እስኪያልፉ ድረስ ሊደበቁባቸው የሚችሉበት ጸጥ ያለ ቦታ ባገኝ ብለው ይመኛሉ።
በመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ ጥናት የምናሳልፈው ጊዜ ውድ እና ያልባከነ ጊዜ ነው። ረጃጅም ክፍሎችን እያጠናችሁ ቢሆን ወይንም ለአንድ ኃጢያት የሚሆን የውጊያ ጥቅስ አሊያም ለመጋቢ አገልግሎትዎ የሚሆኑ ምንባቦች ቢሆኑ በእርግጥም እያንዳንዱ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት “ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማሉ” (2 ጢሞቴዎስ 3፡16)
“እግዚአብሔር ለክብሩ የተከላቸው የጽድቅ ዛፎች እንዲባሉ ለጽዮን አልቃሾች አደርግላቸው ዘንድ፥ በአመድ ፋንታ አክሊልን፥ በልቅሶም ፋንታ የደስታን ዘይት፥ በኀዘንም መንፈስ ፋንታ የምስጋናን መጐናጸፊያ እሰጣቸው ዘንድ ልኮኛል። ” (ኢሳይያስ 61፡3)
ኢየሱስም አለ “መንገዱ ከባድ ነው” (ማቴዎስ 7፡14) በቀደሙት ዘመኖቻችን “ከባድ” ማለት ምን ማለት እንደሆነ የምናውቅ ይመስለን ነበር። ከባድ ጥብቅ የሆነ...
ጨርሰው ያንብቡቻርልስ ስፐርጅን:- ማለት የምፈልገው ነገር ሁሉ ሲጨመቅ ይህ ነው:- ወንድሜ ክርስቶስን ሁልጊዜ ስበክ ። እርሱ ሙሉው ወንጌል ነው ። ማንነቱ ፣ ሹመቱ እና...
ጨርሰው ያንብቡDaily Injera is a Christian ministry which delivers a verse from The Holy Bible each day.
The views and opinions expressed on Daily Injera are solely those of the original authors and our contributors. These views and opinions do not necessarily represent Daily Injera or our Staff.