Tuesday, 19 March 2024
John Piper

John Piper

John Piper is founder and teacher of desiringGod.org and chancellor of Bethlehem College & Seminary. For 33 years, he served as pastor of Bethlehem Baptist Church, Minneapolis, Minnesota. He is author of more than 50 books, including A Peculiar Glory.

አጥብቃችሁ በፈለጋችሁት ጊዜ ልታገኙት የምትችሉት የተስፋ መጠን እጅግ ድንቅ ነው። ተስፋ ደግሞ በሕይወታችን እጅግ አስፈላጊ የሆነ ኃይል ነው። ከእግዚአብሔር የመጨረሻ አሸናፊነት ወደ እኛ የሚፈስስ የደስታ ወንዝ ነው። "የእግዚአብሔር ደስታ ደግሞ ኃይላችን ነው" (ነህምያ 8፡10)። አይደለም በእግዚአብሔር ነገር ልንለመልም ይቅርና ያለተስፋ መኖር አንችልም።

ጳውሎስ ገና ከመወለዱ በፊት እግዚአብሔር ለሐዋርያነት እንደለየው እናውቃለን።

ነገር ግን በእናቴ ማኅፀን ሳለሁ የለየኝ በጸጋውም የጠራኝ እግዚአብሔር በአሕዛብ መካከል ስለ እርሱ ወንጌልን እሰብክ ዘንድ ልጁን በእኔ ሁኔታ ሊገልጥ በወደደ ጊዜ፥ ወዲያው ከሥጋና ከደም ጋር አልተማከርሁም።” (ገላትያ 1፡15-16)

ለመኖር ብቸኛው ምክንያት ትልቅ ስፍራ የሰጣችሁትን ነገር ማሳካት ነው። ማንኛውም ሰው ትልቅ ዋጋ ባለው ነገር ፈንታ ላነሰ ነገር ሲል መቼም ቢሆን ዋጋ መክፈል የለበትም። ትልቅ ዋጋ የምትሰጡት ነገር ምን እንደሆነ ለመወሰን መጣር አለባችሁ። ይሄ ካልሆነ ግን የሥራ ዓይነትን (ወይንም ሌላ ማንኛው ነገርን) ለመምረጥ ምንም ጠቃሚ እርምጃ ወደፊት መራመድ አትችሉም።

አንዳንድ ጊዜ ሃሳባችንን እንደ ውቅያኖስ ሰፊ በሆነው በእግዚአብሔር ሉአላዊነት ውስጥ ልንጨምር ያስፈልገናል። ወደ ውስጥ በሰመጥን ቁጥር ክብደቱ ሊሰማን ይገባል። ወደ እዚህ ሰፊ ውቅያኖስ ቢልየን የአቅርቦት ገባር ወንዞች ይፈስሳሉ። እናም እግዚአብሔር እራሱ ከዘላለም እስከ ዘላለም ያሉ የማይቆጠሩ ሥራዎቹን ሰብስቦ በማይሳሳተው መገለጡ ውስጥ ያፈሳቸዋል። ይናገራል ፣ ያስረዳልም እናም ቃል ይገባል። የሚደንቀውንም ሉአላዊ አቅርቦቱን የተጠበቅን እና ነፃነት የሚሰማን ቦታ ያደርገዋል።

እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ እኔ አምላክህ ነኝና አትደንግጥ አበረታሃለሁ፥ እረዳህማለሁ፥ በጽድቄም ቀኝ ደግፌ እይዝሃለሁ” (ኢሳይያስ 41፡10)።

ኤፌሶን 5፡18 “መንፈስ ይሙላባችሁ እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ ይህ ማባከን ነውና” ይላል።

ከቁጥር 19 እስከ 21 በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ውጤቶች ናቸው። በቁጥር 19 ላይ የሚታየው ውጤት ሙዚቃዊ ነው። በግልጽ እንደሚታየው በክርስቶስ መደሰት በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት አንዱ ምልክት ነው። ነገር ግን ደስታ ብቻ አይደለም። በቁጥር 20 ላይ ምስጋናንም ያጠቃልላል። የማያቋርጥ ስለሁሉም የሚደረግ ምስጋና። (ይህ ማጉረምረምን ፣ ማጉተምተምን ፣ መራርነትን ፣ ብስጭትን ፣ መቆዘምን ፣ ጭንቀትን ፣ ጨፍጋጋነትን እና አሉታዊ አስተሳሰብን ያስቀራል።)

ፓስተር ጆን እንደ ጥያቄ ለደረሰው ኢሜል ምላሽ ከሰጠበት ቃለ መጠይቅ በጽሁፍ የተወሰደ።

ይህን ስጽፍ ወንዶችንም እና ሴቶችንም በማሰብ ነው። ለወንዶች በእርግጥ ግልጽ ነው። በወሲባዊ ምስሎች የሚመጣ ፈተናን ለማጥፋት የሚደረግ ውጊያ አስፈላጊ ነው። ለሴቶች ግን ላይስተዋል ይችላል። ይሁን እንጂ ለእውቅ ሰዎች እና ስለ ግንኙነቶች የሚኖርን ቅዠት አስፍተን ፈተናውን ብናስብ ልክ እንደ ወንዶች ሁሉ ለሴቶችም ታላቅ እንደሆነ ይታየናል። ምኞት ስል ወደ ብልሹ ወሲባዊ ምግባሮች የሚመሩ ሃሳቦች እና መሻቶችን ነው። ልክ ያልሆኑ መሻቶችን በመዋጋት ጊዜ የሚያገለግሉ ስልቶች እኚሁላችሁ። 

ማቴዎስ 6፡14-15 “ለሰዎች ኃጢአታቸውን ይቅር ብትሉ፥ የሰማዩ አባታችሁ እናንተን ደግሞ ይቅር ይላችኋልና፤ ለሰዎች ግን ኃጢአታቸውን ይቅር ባትሉ፥ አባታችሁም ኃጢአታችሁን ይቅር አይላችሁም”።

Page 1 of 2

ምስጋና ለመስጠት 32 ምክንያቶች

እንግሊዛዊው ፓስተር እና የመጽሐፍ ቅዱስ ተንታኝ ማቲው ሄነሪ (1662-1714) ከመሞቱ 2 ዓመት በፊት ስለ ጸሎት መጽሐፍ ጽፎ ነበር። ለጸሎት የሚሆን መንገድ...

Donny Friederichsen - avatar Donny Friederichsen

ጨርሰው ያንብቡ

ላለፈ ሕይወታችሁ ባሮች አይደላችሁም

ክርስትና፣" ለውጥ ይቻላል" ማለት ነው። ጥልቅ የሆነ መሠረታዊ ለውጥ። ቀድሞ ልበ ደንዳኖች እና ደረቅ ልቦች ከነበራችሁ አሁን ልበ ሩህሩህ መሆን ትችላላችሁ። ...

John Piper - avatar John Piper

ጨርሰው ያንብቡ

 

The views and opinions expressed on Daily Injera are solely those of the original authors and our contributors. These views and opinions do not necessarily represent Daily Injera or our Staff.

Newsletter

Subscribe to our newsletter. Don’t miss any article, devotionals or wallpapers.

We do not spam!

You're automatically subscribed to bi-weekly articles and daily devotionals. You can customize your subscription settings here.