ጳውሎስ ገና ከመወለዱ በፊት እግዚአብሔር ለሐዋርያነት እንደለየው እናውቃለን።
“ነገር ግን በእናቴ ማኅፀን ሳለሁ የለየኝ በጸጋውም የጠራኝ እግዚአብሔር በአሕዛብ መካከል ስለ እርሱ ወንጌልን እሰብክ ዘንድ ልጁን በእኔ ሁኔታ ሊገልጥ በወደደ ጊዜ፥ ወዲያው ከሥጋና ከደም ጋር አልተማከርሁም።” (ገላትያ 1፡15-16)
ለመኖር ብቸኛው ምክንያት ትልቅ ስፍራ የሰጣችሁትን ነገር ማሳካት ነው። ማንኛውም ሰው ትልቅ ዋጋ ባለው ነገር ፈንታ ላነሰ ነገር ሲል መቼም ቢሆን ዋጋ መክፈል የለበትም። ትልቅ ዋጋ የምትሰጡት ነገር ምን እንደሆነ ለመወሰን መጣር አለባችሁ። ይሄ ካልሆነ ግን የሥራ ዓይነትን (ወይንም ሌላ ማንኛው ነገርን) ለመምረጥ ምንም ጠቃሚ እርምጃ ወደፊት መራመድ አትችሉም።
የሰው ህይወት በምድር ላይ ብዙ ሰልፍ፣ ብዙ መከራ፣ ብዙ ፈተና እንዳለበት የእግዚአብሔር ቃል ይናገራል። የመከራውም ሆነ የፈተናው ዓይነት ብዛቱም ሆነ ዐይነቱ ከሰው ሰው ይለያይ እንጂ፣ ፈተና በሰው ህይወት ውስጥ ከማይቀሩት እውነታዎች ውስጥ አንዱ ነው።
አልዛይመር በሚባል በሽታ ለብዙ ዓመት ስትሰቃይ ከቆየች በኋላ አያቴ በ2002 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም በሞት ተለየች። የቀሩ ትውስታዎች ቢኖሯትም አብዛኛዎቹ የማስታወስ አቅሟ ግን ደክሞ ነበር።
እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር እንደሆነ መቶ በመቶ ብታምኑ ምን የሚሆን ይመስላችኋል? እንደተቀበላችሁ ብቻ ሳይሆን በክርስቶስ ማንነት እና ሥራ ምክንያት ሙሉ ለሙሉ እንደተቀበላችሁ ብታምኑ? ታላቅ የምትሉት ስኬታችሁ የተለየ ወደ እርሱ እንደማያቀርባችሁ ወይንም የመጨረሻው ውድቀታችሁ የቱንም ከእናንተ እንደማይወስድ ብታምኑስ? ይህን ብታምኑ ፤ በእርግጥ ብታምኑ በሕይወታችሁ ውስጥ ለደስታ ያላችሁን ፍለጋ ሙሉ በሙሉ ይቀይረዋል።
አንዳንድ ጊዜ ሃሳባችንን እንደ ውቅያኖስ ሰፊ በሆነው በእግዚአብሔር ሉአላዊነት ውስጥ ልንጨምር ያስፈልገናል። ወደ ውስጥ በሰመጥን ቁጥር ክብደቱ ሊሰማን ይገባል። ወደ እዚህ ሰፊ ውቅያኖስ ቢልየን የአቅርቦት ገባር ወንዞች ይፈስሳሉ። እናም እግዚአብሔር እራሱ ከዘላለም እስከ ዘላለም ያሉ የማይቆጠሩ ሥራዎቹን ሰብስቦ በማይሳሳተው መገለጡ ውስጥ ያፈሳቸዋል። ይናገራል ፣ ያስረዳልም እናም ቃል ይገባል። የሚደንቀውንም ሉአላዊ አቅርቦቱን የተጠበቅን እና ነፃነት የሚሰማን ቦታ ያደርገዋል።
“እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ እኔ አምላክህ ነኝና አትደንግጥ አበረታሃለሁ፥ እረዳህማለሁ፥ በጽድቄም ቀኝ ደግፌ እይዝሃለሁ” (ኢሳይያስ 41፡10)።
ኤፌሶን 5፡18 “መንፈስ ይሙላባችሁ እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ ይህ ማባከን ነውና” ይላል።
ከቁጥር 19 እስከ 21 በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት ውጤቶች ናቸው። በቁጥር 19 ላይ የሚታየው ውጤት ሙዚቃዊ ነው። በግልጽ እንደሚታየው በክርስቶስ መደሰት በመንፈስ ቅዱስ የመሞላት አንዱ ምልክት ነው። ነገር ግን ደስታ ብቻ አይደለም። በቁጥር 20 ላይ ምስጋናንም ያጠቃልላል። የማያቋርጥ ስለሁሉም የሚደረግ ምስጋና። (ይህ ማጉረምረምን ፣ ማጉተምተምን ፣ መራርነትን ፣ ብስጭትን ፣ መቆዘምን ፣ ጭንቀትን ፣ ጨፍጋጋነትን እና አሉታዊ አስተሳሰብን ያስቀራል።)
“የሰው ልጅ የጠፋውን ሊፈልግና ሊያድን መጥቶአልና” (ሉቃስ 19፡10)
ክርስትና “ኢየሱስ የጠፋውን ሊፈልግና ሊያድን መጥቶአልና” በሚሉት ቃላት ሊጠቃለል ይችላል። የወንጌልንም አንኳር ሃሳብ እንድናስረዳ ብንጠየቅ እንዲሁ ነው።
እንግሊዛዊው ፓስተር እና የመጽሐፍ ቅዱስ ተንታኝ ማቲው ሄነሪ (1662-1714) ከመሞቱ 2 ዓመት በፊት ስለ ጸሎት መጽሐፍ ጽፎ ነበር። ለጸሎት የሚሆን መንገድ...
ጨርሰው ያንብቡትምህርት ሚኒስቴር (የሃገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ) ባሳለፍነው አርብ መስከረም 24 ወደ መንግስት ዩኒቨርሲቲዎች (ከፍተኛ የትምህርት ተቋማ...
ጨርሰው ያንብቡDaily Injera is a Christian ministry which delivers a verse from The Holy Bible each day.
The views and opinions expressed on Daily Injera are solely those of the original authors and our contributors. These views and opinions do not necessarily represent Daily Injera or our Staff.