David Mathis is executive editor for desiringGod.org, pastor at Cities Church in Minneapolis/Saint Paul, and adjunct professor for Bethlehem College & Seminary. He is author of Habits of Grace: Enjoying Jesus through the Spiritual Disciplines.
በመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ ጥናት የምናሳልፈው ጊዜ ውድ እና ያልባከነ ጊዜ ነው። ረጃጅም ክፍሎችን እያጠናችሁ ቢሆን ወይንም ለአንድ ኃጢያት የሚሆን የውጊያ ጥቅስ አሊያም ለመጋቢ አገልግሎትዎ የሚሆኑ ምንባቦች ቢሆኑ በእርግጥም እያንዳንዱ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት “ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማሉ” (2 ጢሞቴዎስ 3፡16)
እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር እንደሆነ መቶ በመቶ ብታምኑ ምን የሚሆን ይመስላችኋል? እንደተቀበላችሁ ብቻ ሳይሆን በክርስቶስ ማንነት እና ሥራ ምክንያት ሙሉ ለሙሉ እንደተቀበላችሁ ብታምኑ? ታላቅ የምትሉት ስኬታችሁ የተለየ ወደ እርሱ እንደማያቀርባችሁ ወይንም የመጨረሻው ውድቀታችሁ የቱንም ከእናንተ እንደማይወስድ ብታምኑስ? ይህን ብታምኑ ፤ በእርግጥ ብታምኑ በሕይወታችሁ ውስጥ ለደስታ ያላችሁን ፍለጋ ሙሉ በሙሉ ይቀይረዋል።
ስለግል የፀሎት ጊዜያችሁ መለስ ብላችሁ የምታዩበት እና በመጪዎቹ ቀናት አንድ ወይንም ሁለት ነገሮችን ለማስተካከል የምታልሙበት ጊዜ አሁን ነው። በተለምዶ ለማደግ እና ረዘም ያለ መንገድን ለማቅናት የተሻለ የሚባለው አማራጭ አጠቃላይ እድሳት ሳይሆን አንድ ወይንም ሁለት የተወሰኑ ችግሮችን ለይቶ ማውጣቱ ነው።
ምንአልባት አልፎ አልፎ አልያም ፈጽሞ ከማይጾሙት ብዙኃኑ የክርስቲያን ጎራ ልትሆኑ ትችላላችሁ። መጽሐፍ ቅዱሳችንን ስላላነበብን ወይንም ከአንድ ሊታመን ከሚገባ ስብከት ስላልተማርን ወይንም ስለጾም ሃይል ስላልሰማን አይደለም። እንደእርሱ ቢሆን እራሱ ልናደርገው አንፈልግም። መብላታችንን ዘወር ማድረጉ ከባድ ነገር ይሆንብናል።
አንዱ ምክንያት ያለንበት ማህበረሰብ ሊሆን ይችላል። ምግብን እንዲሁ ተገናኝቶ ለመብላት እና ግንኙነታችንን ለማሳደግ እንበላለን ወይንም ከኃላፊነት ለመሸሽም እንበላለን።
መጽሐፍ ቅዱሳችንን ልናነብብ ስንከፍት ለብቻችንን አይደለንም ። መንፈስ ቅዱስ ለክርስቶስ ክብር ሲል ልባችንን ሊያነሳሳ አዕምሮአችንን ሊያበራ ሕይወታችንን ሊቀይስ በእግዚአብሔር ቃል ላይ ሰፍፎ አለ (ዮሐንስ 16፡14) ። መጽሐፍ ቅዱስን ለማንበብ ዋነኛው መስፈርት መንፈስ ቅዱስ ነው ። ተራ የሚመስልን ነገር ወደ ኃያል ነገር ይቀይረዋል ። ስለዚህም ለዓይኖቻችን ለአዕምኖአችን እና ለልባችን ሳንጸልይ መጽሐፍ ቅዱስን ስናነብብ ሞኝነት ይሆንብናል ።
የሰው ህይወት በምድር ላይ ብዙ ሰልፍ፣ ብዙ መከራ፣ ብዙ ፈተና እንዳለበት የእግዚአብሔር ቃል ይናገራል። የመከራውም ሆነ የፈተናው ዓይነት ብዛቱም ሆነ ዐይነቱ ...
ጨርሰው ያንብቡDaily Injera is a Christian ministry which delivers a verse from The Holy Bible each day.
The views and opinions expressed on Daily Injera are solely those of the original authors and our contributors. These views and opinions do not necessarily represent Daily Injera or our Staff.