እግዚአብሔራዊ ሕይወት ወደ እግዚአብሔር በማዘንበል የሚኖር ነው። ፊታችንን ከእርሱ ሳይሆን ወደእርሱ ነው የምናዞረው። መገኘቱን ማስተዋላችንን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየወደድነው እንሄዳለን። እናስታውሰዋለን፤ አንረሳውም። በቀኑ መጨረሻ ላይ ተስፋችንን በእርሱ ላይ እንጥላለን። ከሞት እንደሚያድነን ብቻ ሳይሆን በሚቀጥለው ሰዓት እንኳን በእርግጥ እንደሚረዳን በእርሱ እንታመናለን።
ወደ አንድ ሰው ቤት ወይንም የሥራ ቦታ ሄዳችሁ ያንን ሰው ቀርቦ መገኛኘት አስጨንቋችሁ ያውቃል? የምትገናኙበት ጊዜ በደረሰ ጊዜ ልትነግሩት ያሰባችሁት ሁሉ ስትለማመዱት የቆያችሁት ነገር ሁሉ ከጭንቅላታችሁ ውስጥ በንኖ ጠፍቶ መናገር እንደምትችሉ ሁላ እርግጠኛ ላትሆኑ ትችላላቸሁ።
አንድ ወጣት የሚከተለዉን ጥያቄ አስተላልፎልናል፡-
ፓስተር ጆን፣ የሴት ጓደኛዬን እንድታገባኝ ልጠይቃት እፈልጋለሁ። ለትዳርም በምዘጋጅበት ጊዜ የቀደሙት ስህተቶቼ ወደ አዕምሮዬ ይመጣሉ። ከመዳኔ በፊት አብሬአቸሁ የተኛኋቸው ሴቶች እና ጌታ ቢፈቅድ አሁን ከማገባት ሴት ጋር የሰራኋቸውን ስህተቶች ወደኋላ ተመልሼ አስባለሁ። ብዙ ጊዜ ሰዎች ለትዳር መጠበቅ ስላለበት ንፅህና ይህንንም ማባከን እንዴት አስከፊ እንደሆነ ይናገራሉ። እንደኔ ላሉ ከዝሙት ጋር በተያያዘ ፀፀት ለሚኖሩ ወንድና ሴቶች ምን አይነት እውነት ልታካፍለን ትችላለህ?
ትዳራችሁ ምን ያህል ሚቆይ ይመስላችኋል? ሌላ ተጨማሪ አምስት አመት ምትቀጥሉ ይመስላችኋል? አስርስ? ሃምሳ? ከዘላለም ጋር ሲነፃፀር ብዙም እንደማይባል ሁላችንም ምንስማማ ይመስለኛል። ዘላለም ትዳርንም ሆነ በዚህ ዓለም ላይ ያለን ማንኛውንም ነገር የምንደሰትበትን መንገድ ይቀይራል። ዘላለም የፍቅራችንን አቅጣጫ ይቀይራል። ባለቤቴንና ልጆቼን በዚህ ስላለ ህይወት ትኩረታቸውን እንዲያደርጉ ባደርግ ስለመጪው ግን ባላዘጋጃቸው እየወደድኋቸው አይደለም። አንዳንድ ክርስቲያኖች ትዳር ላይ አብዝተው ከማተኮራቸው የተነሳ የክርስትና ዋና ዓላማ በደስተኛ ትዳር ውስጥ መኖር እንደሆነ ይመስላቸዋል። እግዚአብሔርንም የነገሮች ማግኛ መንገድ አድርገው ያስቡታል። ብዙ ክርስቲያኖች ከመስቀሉ ይልቅ ስለ ትዳራቸው እግዚአብሔርን ሲያመሰግኑት እሰማለሁ። እርግጥ ነው አግዚአብሔር ቤተሰቦቻችንን እንድንወድ ይፈልጋል ነገር ግን ጥንቃቄ ልናደርግ ያሻል።
ልቤ ሊደበዝዝ ድርቅ ሲል እና ሲደክም መዝሙር 51 ላይ ወደሚገኝ የዳዊት መዝሙር ዘወር እላለሁ።
በአሁኑ ጊዜ ያለችው ቤተ ክርስትያን መስጠት ላይ ጎበዝ አይደለችም። ይሄ ዜና ሳይሆን በጥናት የተደገፈ እውነታ ነው።
ጨርሰው ያንብቡDaily Injera is a Christian ministry which delivers a verse from The Holy Bible each day.
The views and opinions expressed on Daily Injera are solely those of the original authors and our contributors. These views and opinions do not necessarily represent Daily Injera or our Staff.