Tuesday, 19 March 2024
Naol Befkadu

Naol Befkadu

Naol Befkadu Kebede (BTh, student of MA in Ministry and Medical Doctorate student at AAU) is the founder and contributor of Lechristian Blog, an online ministry that aims to redeem cultures for the glory of God and to inspire and encourage believers for the completion Great Commission. Naol has authored an Amharic book titled "ተነሺ ፤ አብሪ" (2015) that motivates young believers for a meaningful and radical life. 

ትምህርት ሚኒስቴር (የሃገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ) ባሳለፍነው አርብ መስከረም 24 ወደ መንግስት ዩኒቨርሲቲዎች (ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት) የተማሪዎችን ምደባ ይፋ አድርጓል። እንደ ምንጊዜውም ሁሉ ለአንዳንዶች ሲመደብላቸው ለሌሎች ደግሞ ተመድቦባቸዋል። እንደእውነታው ከሆነ ብዝሃው ወደሚፈልግበት ቦታ አይደለም የሚሸኘው። ከዚህ መነሻ ብዙ ክርስቲያን ተማሪዎችም ግር ሲሰኙ እና በተመደቡበት ዩኚቨርሲቲ ለመማር እና ላለመማር ፣ ለመሄድ እና ላለመሄድ እንዲሁም ለመቀየር እና ላለመቀየር ሲያመነቱ ይታያል። ይህ የሚጠበቅ ስሜት ሲሆን እዚህ ላይ ደግሞ የእግዚአብሔር ሃሳብ እና ፈቃድ ምን ሊሆን እንደሚችል እንዲጠይቁ ማበረታታቱ መልካም ነው።

"ይሄ ደሞ ምንድን ነው?" አልኩት በእጄ የሆራ አርሰዲ ዙሪያ ረግረጉን ይዞ የበቀለውን ሳር ቀንጥሼ ውሃው ውስጥ እየነከርኩ። ስለማደርገው ነገር ምንም አልገባኝም። ነገር ግን ይህንን ስርዓት በመፈጸም ከብዙ ሺህ ሰዎች ጋር ተቀላቅያለሁ። ከብዙ ሺህ ሰዎች መካከል ደግሞ ይህንን ስርዓት ከልቡ የሚያከብር ወላጅ አባቴ አለ። አይን አይኔን እያየ ጥያቄዬን ካደመጠ በኋላ "ይህ በኦሮሞ ባህል መሰረት ለምድራችን ለምነት ፈጣሪን የምንማጸንበት ስርአት ነው። ውሃውና ሳሩ የሚወክሉትም ይህንን ነው። ከዚህም በላይ በአባቶች ጸሎት የተመረቀ ውሃ ነው። ለእኛ እንደጸበል ነው" አለኝ።

‹‹እላችኋለሁም ብዙዎች ከምሥራቅና ከምዕራብ ይመጣሉ ከአብርሃምና ከይስሃቅ ከያዕቆብም ጋር በመንግስተ ሰማያት ይቀመጣሉ።›› ማቴ 8፡10-11

አሁን ሃገራችን ስላለችበት ሁኔታ ሳስብ አንድ ነገር ትዝ አለኝ።

ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ የኖረበት ዘመን (የመጀመርያው ክፍለዘመን) ላደገበት የአይሁድ ማህበረሰብ የመረጋጋት እና የሰላም ጊዜ አልነበረም። አይሁዶች በሮም ተገዝተው የነበረበት፣ በዚህም ምክንያት ከዚህ አገዛዝ ነጻ ለመውጣት እየታገሉ የነበረበት ጊዜ ነበር። በዚህም ምክንያት አይሁድ ራሳቸው በዚህ ሃሳብ ተከፋፍለው ነበር። ቀናተኛዎቹ (“Zealots”) የተባሉት የአይሁድ ክንፍ በጦርነት ትግል ሮምን ለመጣል የተነሱ እና ሽምቅ ውጊያ የሚያደርጉ ነበሩ። ፈሪሳውያኑ ደግሞ ሁሉን “አስማምተው” ለመኖር የሚሞክሩ ነበሩ። እንዲሁም ከማህበረሰቡ ተገልለው በበረሃ የሚኖሩ (የመነኑ) የአይሁድ ሰዎችም ነበሩ።

ታዋቂው አሜሪካዊ የወንጌል ሰባኪ ዊልያም ፍራንክሊን ግራሃም ወይም በአጭሩ ቢሊ ግራሃም በ99 አመታቸው ዜና እረፍታቸው በትላንትናው ዕለት (የካቲት 14) ማለዳ ከሳውዝ ካሮሊና ግዛት ከመኖርያ ቤታቸው ተሰምቷል። ይህ መረጃ እንደወጣ ሁለት ወዳጆቼ በሰአታት ልዩነት ደውለው ሲነግሩኝ እጅግ ነበር ያዘንኩት። ደግሞ በአካል አገኛቸው ዘንድ ምኞቴ እንደነበር ወዳጆቼ ስናገር ሰምተውኛል። እኔ በግሌ ከጽሁፍ ለጥቂት ወራት ርቄ የነበረ ቢሆንም የእርሳቸውን ሞት ስሰማ ግን ዝም ማለት አልሆነልኝም።

 

The views and opinions expressed on Daily Injera are solely those of the original authors and our contributors. These views and opinions do not necessarily represent Daily Injera or our Staff.

Newsletter

Subscribe to our newsletter. Don’t miss any article, devotionals or wallpapers.

We do not spam!

You're automatically subscribed to bi-weekly articles and daily devotionals. You can customize your subscription settings here.