ስለ መልካም ዜና ሳስብ ሶስት ጥያቄዎች ወደ አዕምሮዬ ይመጣሉ።
1ኛ መልካም ዜና ለምን ያህል ጊዜ ነው ትኩስ ዜና ሆኖ የሚቆየው?
2ኛ መልካም ዜና ለምን ያህል ጊዜስ ነው መልካም ሆኖ የሚቆየው?
3ኛ መልካም ዜና ሲነገር መልካም ውጤት ብቻ ነው የሚገኘውን?
የሚሉት ጥያቄዎች ናቸው። የሐዋርያው ጳውሎስ የመጨረሻ ቀናት ጽናቱን ከፈተኑት ነገሮች እነዚህ ጥያቄዎች እንደሚኖሩ አልጠራጠርም። የሐዋርያው ጳውሎስ ወንጌል ወይም መልካም ዜና ከላይ ያሉትን ሶስት ጥያቄዎች መመለስ ነበረበት። ሐዋርያው ራሱ እንደሚናገረው የእርሱ ወንጌል ከዳዊት ዘር የሆነው ከሙታን የተነሳው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው (2ኛ ጢሞቴዎስ 2:8) ። የጳውሎስ መልካም ዜና ከሞት የተነሳው ኢየሱስ ነው! ይህን ዜና ከላይ ባሉት ሶስት ጥያቄዎች ብንፈትነው። ጳወሎስ ሶስቱንም ጥያቄዎች እንዲህ ይመልስልናል።
1ኛ ይህ መልካም ዜና ለምን ያህል ጊዜ ነው ዜና ሆኖ የሚቆየው? ለዘላለም! ወንጌል የዘላለም ጉዳይ ነው! (2ኛ ጢሞቴዎስ 1:9)
2ኛ ይህ መልካም ዜና ለምን ያህል ጊዜስ ነው መልካም ሆኖ የሚቀጥለው? ለዘላለም! ወንጌል አሁንም የዘላለም ጉዳይ ነው! (2ኛ ጢሞቴዎስ 2:10)
3ኛ ይህ መልካም ዜና ሲሰበክ መልካም ውጤት ብቻ ነው የሚገኘውን? አይደለም1 መከራም አለ! (2ኛ ጢሞቴዎስ 2:9)
ለሐዋርያው ጳውሎስ በመጨረሻዎቹ ቀናት እንኳን ወንጌል በጊዜ ሂደት የሚለወጥ ነገር አልነበረም። ሐዋርያው ከምንም በላይ ወንጌል መከራን ይዞ ሊመጣ እንደሚችልም ያውቃል። ስለዚህ ወንጌልን እየሰበከ መከራን በጽናት ለማለፍ ቆረጠ ሰው ነበር!
ዛሬ እንደ ሐዋርያው ‹የእኔ› ምንለው ወንጌል ከዳዊት ዘር የሆነው ከሙታን የተነሳው ኢየሱስ ክርስቶስ ከሆነ የሚገጥመን መልካም ውጤት ብቻ ሳይሆን መከራም ከፊት ለፊታችን እንዳለ ማወቅ አለብን። ‹መከራ የለም! › የሚሉ ሰዎች ወንጌላቸው እንደ ሐዋርያው ጳውሎስ ወንጌል ስላልሆነ ብቻ ነው። አንደ ሐዋርያው ጳውሎስ እውነትን የሰበከ ግን መከራ ማየቱ አይቀሬ ነው።
ታዲያ ለሁላችን የሚቀረው ጥያቄ የዘላለም ጉዳይ ለሆነው ለዚህ ወንጌል መከራን እንኳ ለመቀበል ጽኑ ነን ወይ? የሚለው ነው!
ጳውሎስን ከጎኑ ቆሞ ያበረታ እና ያጸና አምላክ (የሐዋርያት ሥራ 23፡11) እኛንም ያበርታን ደግሞም ያጽናን! አሜን!
IntroductionDay 1 Day 2Day 3Day 4Day 5Day 6Day 7Day 8