Tuesday, 19 March 2024

ቀን 2 - "በእስያ አውራጃ ያሉት ሀሉ እንደተዉኝ ታውቃለህ" 2ኛ ጢሞቴዎስ 1:15

Posted On %PM, %04 %833 %2018 %22:%Jun Written by

አንድ የ16ኛው ክፍለዘመን የጀርመን የተሃድሶ አራማጅ የነበሩ የቤተ ክርስቲያን አባት "አለም ሁሉ እኔን ቢቃወመኝ ፤ እኔ ብቻዬን አለምን እቃወማለሁ" ብለው ነበር። ይህ አባባል በዚህ ውሸት በደጋፊ ብዛት ተሞሽራ እውነት በምትመስልበት በ21ኛው ክፍለዘመን የጎላ ትርጉም አለው። እኛም ብንሆን እውነተኞች እንደሆንን የሚሰማን ብዙ ሕዝብ ሲያጅበን ነው። ሰዎች ትተውን ቢሄዱስ?

ሐዋርያው ጳውሎስ በዴማስ ብቻ አይደለም የተተወው። በእስያ አውራጃ ያሉት ሁሉ ትተውት ነበር። እነዚህ "በእስያ አውራጃ ያሉት ሁሉ" ተብለው የተጠቀሱት ምናልባት ሐዋርያው ራሱ ወንጌል የሰበከላቸው እና ያስተማራቸው ሊሆኑ እንደሚችሉ ይታመናል። እነዚህ ሰዎች በመልካም ጊዜ ሐዋርያውን ሲያበረታቱ የነበሩ ሊሆኑ ይችላሉ። አሁን በጨለማ እስር ቤት ውስጥ ሲሆን ግን ሁሉም ተውት? የጳውሎስ ጽናት ምን ያህል ይፈተናል?!

ዛሬ ምንድነው ሰዎች ሁሉ ትተውን ብቻችንን እየተጋፈጥነው ያለው ጉዳይ? ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም እና ስለክርስትና ሕይወት እየተገለልን እና እየተሸፈብን እውነት ከእኛ ጋር የሌለች እስኪመስል ድረስ ሆነን ይሆን? ለእኛ የሐዋርያው ጳውሎስ የመጨረሻ ቀናት እጅግ ትምህርት ይሆኑናል! ጳውሎስ ምንም እንኳ በእሲያ አውራጃ ያሉት ቢተውትም እርሱ ግን ያመነውን እውነት ይዞ እስከመጨረሻው ድረስ በጽናት ተጉዟል!

አንድ የእግዚአብሔር ሰው እንዳሉት ይህ ዘመን ሰዎች ‹በአይናቸው የሚያስቡበት እና በስሜታቸው የሚያዩበት› ዘመን ነው። ብዙ ተከታይ ያለው የትኛውም ነገር እውነተኛ እንደሆነ ይታሰባል። ስሜትን የሚያስደስተውን የትኛውንም ነገር ለማየት ሰዎች ሁሉ ወደ አንድ ቦታ የሚጎርፉበት ጊዜ ነው። በዚህ ጊዜ ስለ ክርስቶስ ስም እና ስለ ጨዋ ክርስቲያናዊ ሕይወት የሚሰደብ እና የሚገፋ ሁሉ በብዙዎች ዘንድ እንደሞኝ ተቆጥሮ ይተዋል። ታዲያ ‹አለም ሁሉ እኔን ቢቃወመኝ ፤ እኔ ብቻዬን አለም እቃወማለሁ› የማለቱ አቅም ይኖረን ይሆን? › 

ጳውሎስን ከጎኑ ቆሞ ያበረታ እና ያጸና አምላክ (የሐዋርያት ሥራ 23:11) እኛንም ያበርታን ደግሞም ያጽናን! አሜን!

 

 IntroductionDay 1 Day 2Day 3Day 4Day 5Day 6Day 7Day 8

 

Subscribe to get our devotionals to your email, everyday!

መንገዱ ከባድ ነው።እርሱ ግን ጠንካራ ነው።

ኢየሱስም አለ “መንገዱ ከባድ ነው” (ማቴዎስ 7፡14) በቀደሙት ዘመኖቻችን “ከባድ” ማለት ምን ማለት እንደሆነ የምናውቅ ይመስለን ነበር። ከባድ ጥብቅ የሆነ...

Jon Bloom - avatar Jon Bloom

ጨርሰው ያንብቡ

የተሰራችሁት ወደ እግዚአብሔር ለሚያዘነብል ሕይወት ነው

እግዚአብሔራዊ ሕይወት ወደ እግዚአብሔር በማዘንበል የሚኖር ነው። ፊታችንን ከእርሱ ሳይሆን ወደእርሱ ነው የምናዞረው። መገኘቱን ማስተዋላችንን ከጊዜ ወደ ጊዜ እ...

John Piper - avatar John Piper

ጨርሰው ያንብቡ

 

The views and opinions expressed on Daily Injera are solely those of the original authors and our contributors. These views and opinions do not necessarily represent Daily Injera or our Staff.

Newsletter

Subscribe to our newsletter. Don’t miss any article, devotionals or wallpapers.

We do not spam!

You're automatically subscribed to bi-weekly articles and daily devotionals. You can customize your subscription settings here.