Tuesday, 19 March 2024

ቀን 3 - "አንጥረኛው እስክንድሮስ ብዙ ጉዳት አድርሶብኛል፤… መልዕክታችንን እጅግ ተቃውሟልና" 2ኛ ጢሞቴዎስ 4:14-15

Posted On %PM, %05 %834 %2018 %22:%Jun Written by

የእውነተኛ ክርስቲያናዊ አገልግሎት ዋና መለያው ተቃውሞ መኖሩ ነው። የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ስናጠና በዘመናት መሃል የተነሱትን የእምነት አባቶች የሚያመሳስላቸው ነገር ቢኖር ሁሉም ተቃውሞን ተጋፍጠው ማለፋቸው ነው። ለአውግስጢን - ጴላጂየስ ፣ ለማርቲን ሉተር - ጆን ታትዚል ፣ ለአባ እስጢፋኖስ - አጼ ዘረ ያዕቆብ ወዘተ እያልን የእምነት አባቶች እና ተቃዋሚዎቻቸውን መዘርዘር እንችላለን። ተቃውሞ ልብን ይሰብራል። ተቃውሞ እምነትን ይፈትናል። ተቃውሞ ጽናትን ይጠይቃል። በተለይ እነዚህ ተቃውሞዎች ከውጭ ብቻ ሳይሆኑ ከቤተ ክርስቲያን ውስጥም ጭምር መምጣታቸው ጫናውን በክርስቲያኖች ላይ ያጎላዋል።   

ሐዋርያው ጳውሎስ በሮም እስር ቤት ሆኖ ጽናቱን ከፈተኑት ጉዳዮች መካከል እነዴማስ አለምን ወደው እርሱን መተዋቸው ብቻ አይደለም። በእስያ ያሉት ሁሉ ጳውሎስን መተዋቸው ብቻም አልነበረም። ነገር ግን በግልጽ ጳውሎስን እና የእርሱን ትምህርት የሚቃወሙ ሰዎች ነበሩ። ከእነርሱም መካከል አንጥረኛው እስክንድሮስ በስም ተጠቅሷል (2ኛ ጢሞቴዎስ 4:14)። አንጥረኛው እስክንድሮስ ምናልባት መዳብ በማንጠር ሙያው የታወቀ ሊሆን እንደሚችል ይታመናል። ነገር ግን ሐዋርያው ጳውሎስ ላይ ብዙ ጉዳት አድርሶበታል። አካላዊ ጉዳት ያድርስበት አያድርስበት ግልጽ ባይሆንም ስነልቦናዊ ጉዳት እንዳደረሰበት ግን እርግጥ ይመስላል። ከዚህም በላይ እስክንድሮስ ጳውሎስን እየተከታተለ ይቃወመው እንደነበርም ከክፍሉ መረዳት ይቻላል።

ዛሬ የእኛ እስክንድሮስ ይኖረን ይሆን? ልባችንን በተቃውሞ እያቆሰለ ፤ ስማችንን በመጥፎ እያነሳ ፤ ሰዎችን በእኛ ላይ እያሳመጸበን ያለ የመልዕክታችን ተቃዋሚ ይኖር ይሆን? ተቃዋሚዎች በእርግጥ ጽናታችንን ይፈታተኑታል። ሁሉንም እርግፍ አድርገን እንድንተው ሊጋብዙን ይችላሉ። ወይም ወዳልሆነ የጠብ አቅጣጫ ሊጎትቱን ይችላሉ። ሐዋርያው ጳውሎስ ግን በተቃውሞ ፊት ያውም በእስርቤት ጽኑ ነበር!

ሐዋርያው ያልተፈለገ ምላሽንም ለመስጠት አለፈለገም። ይልቅስ ሁሉንም ለእግዚአብሔር አሳልፎ ሲሰጥ እናነባለን (2ኛ ጢሞቴዎስ 4:14) ። እኛስ ሁሉን ለእግዚአብሔር አሳልፈን ሰጥተን ተልዕኳችንን እና መልዕክታችንን ሳንለውጥ በተቃዋሚዎች ፊት ጸንተን መቆም እንችላለን?

ጳውሎስን ከጎኑ ቆሞ ያበረታ እና ያጸና አምላክ (የሐዋርያት ሥራ 23:11) እኛንም ያበርታን ደግሞም ያጽናን! አሜን!

 

 IntroductionDay 1 Day 2Day 3Day 4Day 5Day 6Day 7Day 8

 

Subscribe to get our devotionals to your email, everyday!

የተስፋ ነፀብራቆች ሁኑ

“ስለዚህ እናንተ ደግሞ እንደምታደርጉ፥ እርስ በርሳችሁ ተመካከሩ አንዱም አንዱም ሌላውን ያንጸው” (1 ተሰሎንቄ 5፡11)። “ትውልዱም የቆጵሮስ ሰው የነበረ ...

Jon Bloom - avatar Jon Bloom

ጨርሰው ያንብቡ

ላለፈ ሕይወታችሁ ባሮች አይደላችሁም

ክርስትና፣" ለውጥ ይቻላል" ማለት ነው። ጥልቅ የሆነ መሠረታዊ ለውጥ። ቀድሞ ልበ ደንዳኖች እና ደረቅ ልቦች ከነበራችሁ አሁን ልበ ሩህሩህ መሆን ትችላላችሁ። ...

John Piper - avatar John Piper

ጨርሰው ያንብቡ

 

The views and opinions expressed on Daily Injera are solely those of the original authors and our contributors. These views and opinions do not necessarily represent Daily Injera or our Staff.

Newsletter

Subscribe to our newsletter. Don’t miss any article, devotionals or wallpapers.

We do not spam!

You're automatically subscribed to bi-weekly articles and daily devotionals. You can customize your subscription settings here.