Tuesday, 19 March 2024

ቀን 1 - "ዴማስ ይህን ዓለም ወዶ ትቶኝ ወደ ተሰሎንቄ ሄዷልና" 2ኛ ጢሞቴዎስ 4:10

Posted On %PM, %03 %827 %2018 %21:%Jun Written by

በኮሚኒሰት ደርግ አገዛዝ በእምነታቸው ምክንያት ብዙ መከራ ከተቀበሉ ኢትዮጵያውያን ወንድሞች መካከል አንዱ ሲናገር እንደሰማሁት በደርግ ወቅት መከራን ከተቀበሉ ክርስቲያኖች መካከል ዛሬ በነጻነቱ ዘመን ከእምነታቸው ያፈገፈጉ አሉ። አብረው ብዙ ተጉዘዋል። አብረው ተንገላተዋል፣ ተሰደዋል፣ ተገርፈዋል፣ ቆስለዋል ስለወንጌል ሲሉ መከራን ተቀብለዋል። ዛሬ ግን በነጻነት እና በድሎት ዘመን በጽናት መቆም ተስኗቸዋል።

ሐዋርያው ጳውሎስ በሮሜ የጨለማ እስር ልቡን ሊጎዳ እና ጽናቱን ሊፈታተን ከሚችለው አንዱ ገጠመኝ የዴማስ አለምን ወዶ ጳውሎስን ትቶ ወደ ተሰሎንቄ መሄዱ ነው። ዴማስ በአንድ ወቅት ከጳውሎስ ጋር የነበረ የአገልግሎት አጋሩ ነበር። ለዚህም ማረጋገጫ የሚሆነን ሐዋርያው በሌላኛው ደብዳቤው ላይ ዴማስን ከማርቆስ እና ከሉቃስ ጋር አብሮ መጥቀሱ ነው (ፊልሞና 1:24) ። ታዲያ ጳውሎስ በሁለተኛው እስር ላይ እያለ ዴማስ ጳውሎስን ትቶ አለምን ወዶ በጊዜው ትልልቅ ከሚባሉት ከተሞች ተርታ ወደምትመደበው ወደ ተሰሎንቄ ሄዷል። ብዙ መጸሐፍ ቅዱስ አንባቢያን እንደሚስማሙበት ምናልባት ዴማስ ጳውሎስን ትቶ ተሰሎንቄን የመረጠው በገንዘብ ፍቅር ተነድፎ ሊሆን ይችላል። እንዲያ ከሆነ ደግሞ ዴማስ ጳውሎስን ብቻ ሳይሆን ጌታንም ትቶ ነው የሸሸው።

ወዳጆች ሆይ በድሎት እና በነጻነት ዘመን ሳለን የሚከዱን ይጎዱናል። ነገር ግን እንደ ጳውሎስ በመከራ ውስጥ ሳለን የሚከዱን ምን ያህል ልባችንን ይሰብሩታል? ዘመናችንን ከኖርንለት እና ከተሰደድንለት ወንጌል የቅርብ ወዳጆቻችንን መከራን ፈርተው አልያም ገንዘብን ወደው ከእኛም ከጌታም ሲርቁ ማየት ጽናታችንን ይፈታተነዋል። ነገር ግን ሐዋርያው አሁንም ጽኑ ነበር! ስለተረዳው እውነትም ሆነ ስለተቀበለው አገልግሎት አላመቻመቸም። አስቀድሞም እምነቱ በስጋ እና ደም ምክክር ላይ አልተመሰረተም (ገላትያ 1:12) ። 

ዛሬ እንደ ሐዋርያው አይነት መከራ አይነት ባይሆንም መከራ ግን አለ። በመከራ ውስጥ ጽናታችን የሚፈተነው አንድም የምናውቃቸው ሰዎች ትተውን ሲሄዱ እኛ ለመልእክታችን እና ለጥሪያችን ታማኝ ስንሆን ነው። ክርስቶስን እናገለግላለን ለምንል ሁሉ ይህ መልዕክት ነው! የቅርብ የአገልግሎት አጋራችን ቢያፈገፍግ እኛ በጽናት አንቆያለን?

ጳውሎስን ከጎኑ ቆሞ ያበረታ እና ያጸና አምላክ (የሐዋርያት ሥራ  23:11) እኛንም ያበርታን ደግም ያጽናን! አሜን

 

 IntroductionDay 1 Day 2Day 3Day 4Day 5Day 6Day 7Day 8

 

Subscribe to get our devotionals to your email, everyday!

የእግዚአብሔር ጸጋ ከአዕምሮ በላይ ነው

መጽሀፍ ቅዱስ እግዚአብሔር ቸር አምላክ እንደሆነ ይናገራል። ብዙ ሰዎች ግን ይህንን ለማመን ይቸገራሉ። አንዳንዶች ጸጋ ምን እንደሚመስል ሲያስቡ ይገረማሉ። የእ...

Phillip Holmes - avatar Phillip Holmes

ጨርሰው ያንብቡ

በርባን እና እኔ

ህዝቡ ሁሉ የኢየሱስን መሰቀል ይጠይቃል። በትረካው ውስጥ ማንን አያችሁ?

David Mathis - avatar David Mathis

ጨርሰው ያንብቡ

 

The views and opinions expressed on Daily Injera are solely those of the original authors and our contributors. These views and opinions do not necessarily represent Daily Injera or our Staff.

Newsletter

Subscribe to our newsletter. Don’t miss any article, devotionals or wallpapers.

We do not spam!

You're automatically subscribed to bi-weekly articles and daily devotionals. You can customize your subscription settings here.