ወደ እግዚአብሔር በቀረብንበት በዚያ ስፍራ ከመገኘቱ ጋር ደግሞ እንገናኛለን። በተዘረጉ እጆቹ ሊቀበለን ተዘጋጅቶ እናገኘዋለን። መገኘቱ ሊሰማን እንደሚገባ ከተሰማን በቅድስናው ታላቅነት ልንሸፈን እንችላለን። ይህን ደግሞ ኢሳይያስ ከእግዚአብሔር ጋር ሲገናኝ ከሆነው ማየት እንችላለን።
እንደምን አላችሁ?
ጥፋተኛ ብሆንም እነዚህ ቃላት እንደ ጥያቄ ሳይሆን እንደ ሠላምታ ሲቀርቡልኝ ትንሽ ይረብሸኛል። ተጨባጭ መልስ ሳንፈልግ “እንዴት ናችሁ?” ብሎ መጠየቅ ቀላል ነገር። አንዳንድ ጊዜ ሰዎች ከእርምጃቸው እንኳን ሳያቋርጡ ደህና ነህ? ብለውኝ ያልፋሉ። በእነዚህ ጊዜያት ብቸኛው ተገቢ መልስ “ደህና ነኝ” ነው የሚሆነው ምንም እንኳን ነገሮች ላይሆኑ ቢችሉም። የዚህ አይነቱ ጥልቅ ያልሆነ ሰላምታ ብዙውን የየዕለት መስተጋብራችንን ይሸፍናል። ግንኙነቶቻችንን ብዙ ጊዜ ከላይ ከላይ እንፈጽማለን ነገር ግን ወደ ልባችን ስላለበት ትክክለኛ ሁኔታ ጠልቀን አንገባም።
“ነገር ግን እግዚአብሔር በምሕረቱ ባለ ጠጋ ስለ ሆነ፥ ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን፥ በጸጋ ድናችኋልና”። (ኤፌሶን 2፡4-5)
“ነገር ግን እግዚአብሔር” የሚሉት እኚህ 3 ቃላት በወንጌል የተትረፈረፉ ናቸው። እንደኔና እንደእናንተ ላሉት ጠፍተው ለነበሩ፤ እራሳቸውን ከእግዚአብሔር ላይ ከተደቀነ አመፃ ሊያድኑ የማይችሉ ኃጢያተኞች ከእነዚህ የዘለሉ ሌላ ሦስት የተስፋ ቃላት ላይኖሩን ይችላል።
ጳውሎስ ገና ከመወለዱ በፊት እግዚአብሔር ለሐዋርያነት እንደለየው እናውቃለን።
“ነገር ግን በእናቴ ማኅፀን ሳለሁ የለየኝ በጸጋውም የጠራኝ እግዚአብሔር በአሕዛብ መካከል ስለ እርሱ ወንጌልን እሰብክ ዘንድ ልጁን በእኔ ሁኔታ ሊገልጥ በወደደ ጊዜ፥ ወዲያው ከሥጋና ከደም ጋር አልተማከርሁም።” (ገላትያ 1፡15-16)
የሰው ህይወት በምድር ላይ ብዙ ሰልፍ፣ ብዙ መከራ፣ ብዙ ፈተና እንዳለበት የእግዚአብሔር ቃል ይናገራል። የመከራውም ሆነ የፈተናው ዓይነት ብዛቱም ሆነ ዐይነቱ ከሰው ሰው ይለያይ እንጂ፣ ፈተና በሰው ህይወት ውስጥ ከማይቀሩት እውነታዎች ውስጥ አንዱ ነው።
አልዛይመር በሚባል በሽታ ለብዙ ዓመት ስትሰቃይ ከቆየች በኋላ አያቴ በ2002 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም በሞት ተለየች። የቀሩ ትውስታዎች ቢኖሯትም አብዛኛዎቹ የማስታወስ አቅሟ ግን ደክሞ ነበር።
እግዚአብሔራዊ ሕይወት ወደ እግዚአብሔር በማዘንበል የሚኖር ነው። ፊታችንን ከእርሱ ሳይሆን ወደእርሱ ነው የምናዞረው። መገኘቱን ማስተዋላችንን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየወደድነው እንሄዳለን። እናስታውሰዋለን፤ አንረሳውም። በቀኑ መጨረሻ ላይ ተስፋችንን በእርሱ ላይ እንጥላለን። ከሞት እንደሚያድነን ብቻ ሳይሆን በሚቀጥለው ሰዓት እንኳን በእርግጥ እንደሚረዳን በእርሱ እንታመናለን።
አቤቱ፥ ንጹሕ ልብን ፍጠርልኝ፥ የቀናውንም መንፈስ በውስጤ አድስ። ከፊትህ አትጣለኝ፥ ቅዱስ መንፈስህንም ከእኔ ላይ አትውሰድብኝ። የማዳንህን ደስታ ስጠኝ፥ በእሽታ መንፈስም ደግፈኝ። (መዝሙር 51፡10-12)
የዚህን መልስ ማወቅ ሁላችንም እንፈልጋለን አይደል? ከዚህ በላይ ውጥረትን ሊፈጥር የሚችል ርዕስ ሊኖር ይችላል? ስለፈጠረን ፣ ደግሞም በሕይወት እያቆየን ስላለው ፣ ሊያድነን ልጁን ስለሰጠን ስለ ስለ ሉአላዊው እግዚአብሔር እያወራን ነው። በሰጠን እንፋሎት በሆነች በዚህች ሕይወት ውስጥ ምን እንድናርግለት ይፈልጋል?
የእግዚአብሔርን ሞራላዊ (ግብረ ገባዊ) እና ሉአላዊ ፍቃዶች መለየት እንድትችሉ ልረዳችሁ እፈልጋለሁ። ቀጥሎ ባሉት ሁለት ሃሳቦች መሀከል ያለውን ተቃርኖ መረዳት እንድትችሉ ይረዳችኋል።
ከፖርኖግራፊ ሱስ መውጣት ይቻላል! ክፍል 3 - ከፖርኖግራፊ ሱስ እንዴት መውጣት ይቻላል? በዚህ ተከታታይ ፅሁፍ የመጀመሪያ ክፍል ላይ ‘ፖርኖግራፊ’ ሰዎችን...
ጨርሰው ያንብቡእንግሊዛዊው ፓስተር እና የመጽሐፍ ቅዱስ ተንታኝ ማቲው ሄነሪ (1662-1714) ከመሞቱ 2 ዓመት በፊት ስለ ጸሎት መጽሐፍ ጽፎ ነበር። ለጸሎት የሚሆን መንገድ...
ጨርሰው ያንብቡDaily Injera is a Christian ministry which delivers a verse from The Holy Bible each day.
The views and opinions expressed on Daily Injera are solely those of the original authors and our contributors. These views and opinions do not necessarily represent Daily Injera or our Staff.