Tuesday, 19 March 2024

ነገር ግን እግዚአብሔር…

Posted On %AM, %08 %041 %2017 %03:%Jan Written by

ነገር ግን እግዚአብሔር በምሕረቱ ባለ ጠጋ ስለ ሆነ፥ ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን፥ በጸጋ ድናችኋልና”። (ኤፌሶን 2፡4-5)

ነገር ግን እግዚአብሔር” የሚሉት እኚህ 3 ቃላት በወንጌል የተትረፈረፉ ናቸው። እንደኔና እንደእናንተ ላሉት ጠፍተው ለነበሩ፤ እራሳቸውን ከእግዚአብሔር ላይ ከተደቀነ አመፃ ሊያድኑ የማይችሉ ኃጢያተኞች ከእነዚህ የዘለሉ ሌላ ሦስት የተስፋ ቃላት ላይኖሩን ይችላል። 

ቀድሞ ለእግዚአብሔር ከሚሆን ማንኛውም አይነት ፍቅር ሞተን ግራ ከሚያጋባው ዕውርነታችን ስር ተቀብረን ነበር (ኤፌሶን 2፡1) ፤ ነገር ግን እግዚአብሔር . . . ። ቀድሞ ለእራሳችን ክብር እና የራሳችን ጌታ ለመሆን ባለን ምኞት ተታልለን ነበር፤ ቀድሞ በአየር ላይ ሥልጣን ባለው አለቃ ሳናውቅ እንመራ ነበር (ኤፌሶን 2፡2) ነገር ግን እግዚአብሔር . . . ። ቀድሞ በሥጋችን እና በአዕምሮአችን የስሜት ማዕበል እንግልት እየተነዳን ለሥጋችን ምኞት ተገዢዎች ነበርን (ኤፌሶን 2፡3) ነገር ግን እግዚአብሔር . . . ። ቀድሞ የእግዚአብሔር ጠላቶች ነበርን (ሮሜ 5፡10) እንጠላው ነበር (ሮሜ 1፡30) የቁጣ ልጆች ነበርን። ነገር ግን እግዚአብሔር . . .

ነገር ግን እግዚአብሔር በምሕረቱ ባለ ጠጋ ስለ ሆነ ከአዕምሮ በላይ የሆነ ፍቅሩን ያሳይ ዘንድ ከእግዚአብሔር ተለይተን የሞተነውን፣ እግዚአብሔርን የማንፈልገውን፣ ከእግዚአብሔር ጋር የምንፎካከረውን፣ እግዚአብሔርን የምንጠላውን አጥንታቸው የደረቁ የቁጣ ልጆችን “በሕይወት ኑሩ” (ሕዝቅአል 37፡5) አለን። ለእውነተኛ ውበት፣ ለእውነተኛ ክብር፣ ለእውነተኛ ተስፋ፣ ለእውነተኛ ደስታ እና ፍስሐ ኑሩ አለን! ለእግዚአብሔር ኑሩ አለን (ገላትያ 2፡19) እናም ለዘለዓለም ኑሩ አለን (ዮሐንስ 6፡58)!

ይህንንም ያሳካው ከእግዚአብሔር ተለይተን እንድንሞት ያደረገውን፣ እግዚአብሔርን እንዳንፈልግ የሚያደርገውን፣ ከእግዚአብሔር ጋር እንድንፎካከር የሚያደርገውን፣ እግዚአብሔርን እንድንጠላ የሚያደርገውን፣ የእግዚአብሔርን ቁጣ የሚያስነሳውን ይህን ኃጢያታችንን ሕይወት በሆነው ልጁ ላይ (ዮሐንስ 14፡6) አድርጎ ገደለው (ሮሜ 5፡8)። ስለዚህ እኛ በእርሱ ሆነን የእግዚአብሔር ጽድቅ እንሆን ዘንድ ኃጢያትን የማያውቀው እርሱ — ጻድቁን ለኃጢያተኞቹ — ስለእኛ፤ የእኛ ኃጢያታችን ሆነልን (2 ቆሮንቶስ 5፡21፤ 1 ጴጥሮስ 3፡18)። ለዘለአለም መኖር እንችል ዘንድ ይህን አደረገ (ዮሐንስ 3፡16) ።

እነዚህ “ነገር ግን እግዚአብሔር” የሚሉ ሦስት ቃላት በእግዚአብሔር ጸጋ ብቻ እንደዳንን ይነግሩናል። የሞቱ የቁጣ ልጆች በሕይወት ያሉ የእግዚአብሔር ልጆች ብቻ ሳይሆን የሆኑት ለእርሱም ነው።

በእነዚህ ሦስት ቃላት ፌሽታን አድርጉ። አሁን ካላችሁበትና አስክትሞቱ ባላው ጊዜ ውስጥ የሚፈጠርን ጣፋጭ ሆነ መራራ ክስተት እግዚአብሔር ለበጎ ነገር ይቀይረዋል። (ሮሜ 8፡28) ወደፊትም በእርሱ ዘንድ ባለው ዘላለማዊ ሕይወታችሁ የምታሳልፉት የከበረ ደስታ (መዝሙር 16፡11) “ነገር ግን እግዚአብሔር” ከሚሉት ከእነዚህ ሦስት ቃላት የሆነ ነው።

 

Originally Posted at DesiringGod.org, Translated by Joshua Terefe


 

Last modified on %PM, %22 %791 %2017 %21:%Jan
Jon Bloom

Jon Bloom serves as author, board chair, and co-founder of Desiring God. He is author of three books, Not by Sight, Things Not Seen, and Don’t Follow Your Heart. He and his wife live in the Twin Cities with their five children.

https://twitter.com/Bloom_Jon

ኢየሱስ ያድናል

“የሰው ልጅ የጠፋውን ሊፈልግና ሊያድን መጥቶአልና” (ሉቃስ 19፡10) ክርስትና “ኢየሱስ የጠፋውን ሊፈልግና ሊያድን መጥቶአልና” በሚሉት ቃላት ሊጠቃለል ይች...

Jonathan Parnell - avatar Jonathan Parnell

ጨርሰው ያንብቡ

ምስጋና ለመስጠት 32 ምክንያቶች

እንግሊዛዊው ፓስተር እና የመጽሐፍ ቅዱስ ተንታኝ ማቲው ሄነሪ (1662-1714) ከመሞቱ 2 ዓመት በፊት ስለ ጸሎት መጽሐፍ ጽፎ ነበር። ለጸሎት የሚሆን መንገድ...

Donny Friederichsen - avatar Donny Friederichsen

ጨርሰው ያንብቡ

 

The views and opinions expressed on Daily Injera are solely those of the original authors and our contributors. These views and opinions do not necessarily represent Daily Injera or our Staff.

Newsletter

Subscribe to our newsletter. Don’t miss any article, devotionals or wallpapers.

We do not spam!

You're automatically subscribed to bi-weekly articles and daily devotionals. You can customize your subscription settings here.