ለአስቸጋሪ ሥራዎች እጆቼን ለማበርታት ደጋግሜ የተጠቀምኩበት እንደዚህ ያለ ጥቅስ ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያለ አይመስለኝም። አዕምሮዬ ውስጥ የሚስተጋባው ድምጽ ይህ ነው። ከማንኛውም ጥቅስ በላይ ለብዙ አስርት ዓመታት አገልግሎኛል። ግር የሚሉ ቦታዎች ጋር ስሄድ ፣ አዲስ ቋንቋ ስናገር ፣ የዶክትሬት ትምህርት ፈተናዬን ስወስድ ፣ ለሥራ ቃለ መጠይቅ ሲኖርብኝ ፣ ለብዙ ሕዝብ ስሰብክ ፣ ለካንሰር በሽታ ቀዶ ሕክምና ሲደረግልኝ ፣ ደስ የማይሉ ስልክ ጥሪዎችን ሳደርግ እና ይቅርታ ልጠይቅ ስል አበርትቶኛል።
ይሄን ክፍል ጠቃሚ ከሚያደርጉት ምክንያቶች ውስጥ አንደኛው ስለ እግዚአብሔር በሦስተኛ መደብ (እርሱ ያበረታሀል ይረዳሃል…) ሳይሆን በአንደኛ መደብ (አበረታሃለሁ ፣ እረዳሃለሁ… ) ስለሚናገር ነው። ሁልጊዜ ስለው ለእራሴ በቀጥታ ሲናገረኝ ይሰማኛል። ይህ በሚደንቅ ሁኔታ ኃይል አለው። ከአጠገቤ ሆኖ “ሂድ፤ የምታደርገውን አድርግ እኔ እረዳሀለሁ። አቅምን እሰጥሃለሁ። እደግፍሃለሁ።” እንደሚል አይነት ይሰማኛል።
ሌላ ጠቃሚ የሚሆንበት ምክንያት ደግሞ ሁሉንም ሊያጠቃልል መቻሉ ነው። “እረዳሃለሁ” ለማንኛውም ሁኔታ ሊሆን ይችላል። ሁልጊዜ ደግሞ እርዳታ ያስፈልገኛል። ስለዚህ ይህ ተስፋ ሁልጊዜ ለሁኔታዎቻችን ሁሉ የሚመጥን ነው፤ ላያስፈልገን የሚችልበት ሁኔታ የለም።
ይሄን ክፍል ጠቃሚ ከሚያደርጉት ምክንያቶች ውስጥ አንደኛው ስለ እግዚአብሔር በሦስተኛ መደብ (እርሱ ያበረታሀል ይረዳሃል…) ሳይሆን በአንደኛ መደብ (አበረታሃለሁ ፣ እረዳሃለሁ… ) ስለሚናገር ነው። ሁልጊዜ ስለው ለእራሴ በቀጥታ ሲናገረኝ ይሰማኛል። ይህ በሚደንቅ ሁኔታ ኃይል አለው። ከአጠገቤ ሆኖ “ሂድ፤ የምታደርገውን አድርግ እኔ እረዳሀለሁ። አቅምን እሰጥሃለሁ። እደግፍሃለሁ።” እንደሚል አይነት ይሰማኛል።
ሌላኛው ጠቃሚ ምክንያት ደግሞ በእግዚአብሔር የጽድቅ ባህሪው ክፍሉን ስለሚዘጋው ነው። የእግዚአብሔር ጽድቅ ክብሩን ለማምጣት የሚያደርገው ጠንካራ መሰጠት ነው። ከዛ መንገድ ተዛንፎ አያውቅም። ስለዚህ የስሙ ክብር አደጋ ላይ ባለበት በሚመስል ቦታ ሁሉ በቅንዓት እንደሚገለጥ እርግጥ ነው። ለእምነታችንም ዋስትናው ይህ ነው። በጣም ብዙ መቶዎች ጊዜ አግዞኛል።
በመጨረሻም ይህ ክፍል ጠቃሚ የሚሆነው ምንም እንኳን ለአይሁዶች የታቀደ ቢሆንም ለእኔ ለአሕዛቡም ስለሚሰራ ነው። ይህም የሚሆንበት ምክንያት እግዚአብሔር ለሰጠው የተስፋ ቃል ሁሉ አዎን ማለት በ መሲሁ ኢየሱስ ናቸውና (2 ቆሮንቶስ 1፡20)። ይህም ማለት በወንጌል ምክንያት የእኔ ነው። በእርሱ ለሆኑት ሁሉ ይህ ተስፋ እውነት እንዲሆን ክርስቶስ ሞቷል። በማመኔ ምክንያት በእርሱ ነኝ። ስለዚህ ይህንን ተስፋ ጨምሮ ሌሎች ሁሉም ተስፋዎች የእኔ ናቸው። ለሞተው ደግሞም ለተነሳው ልጁ ታማኝ እንደነበረ ለዚህም ተስፋ የታመነ ይሆናል። የዚህን ያህል እርግጥ ነው።
የእኛ እግዚአብሔር፤ ባለፈ ቀን ረዳታችን
ለመጪው ዘመን ተስፋችን
ከኃይለኛው ወጀብ መጠለያ
የዘላለም ቤታችን ማረፊያ
Originally Posted at DesiringGod.org, Translated by Joshua Terefe