ዊልሰን የተናገረው ነገር ስል እና ጠንካራ ነው።ግን ለምን? በመታዘዝ እና በደስታ መሃከል ያለው መሠረታዊ ግንኙነት ምንድን ነው?
ስለዚህ የሚናገር አንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል በ 1 ዮሐንስ 5፡3-4 ላይ አለ፡-
"ትእዛዛቱን ልንጠብቅ የእግዚአብሔር ፍቅር ይህ ነውና፤ ትእዛዛቱም ከባዶች አይደሉም።ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ዓለምን ያሸንፋልና፤ ዓለምንም የሚያሸንፈው እምነታችን ነው።"
ጆን ፓይፐር በመጨረሻ ህያው ሆንኩ (Finally Alive) በሚለው መጽሐፉ በዚህ ጥቅስ ውስጥ ሦስት ተያያዥ ሀሳቦችን ያሳያል፡-
የመጀመሪያው ተያያዥ ሀሳብ:- “ለእግዚአብሔር ያለን ፍቅር ሸክም ባልሆነ መንፈስ ለትዕዛዛቱ በምናደርገው ታዛዥነት ይገለጻል።”
ሁለተኛው ተያያዥ ሀሳብ:- “ለእዚህ እሺታ ታዛዥነት መሠረቱ ዓለምን ለማሸነፍ አቅም የሚሆነን የአዲስ ውልደት ኃይል ነው።”
ሦስተኛው ተያያዥ ሀሳብ:- “ዓለምን የሚያሸንፈው ኃጢያትን የሚሰብረውና የእግዚአብሔርን ፍቃድ ውብ እንጂ ሸክም እንዳይሆንብን የሚያደርገው እምነታችን ነው።”
ወንጌል ፣ አዲስ ውልደት ፣ እምነት እና በደስታ መታዘዝ አንድ ላይ የሚመጡት እዚህ ጋር ነው። ፓይፐር ተያያዥ ሀሳቦቹን እንደዚህ አያይዞ ያስቀምጣቸዋል ፡-
እምነት የሚያብለጨልጨውን የዓለምን የባርነት መተብተቢያ ይሰብራል። በዚህ መንገድ እምነት በነፃነት እና በደስታ ወደመታዘዝ ይመራናል። እግዚአብሔር እና ቅዱሱ ውብ እንጂ ሸክም አይሆኑብንም። አዲሱ ልደት የዓይኖቻችንን መሸፈኛ አንስቷል። አሁን የነገሮችን እውነተኛ ማንነት ማየት እንችላለን። በደስታ ለመታዘዝ አሁን ነፃ ነን።
ስለዚህ ነው የቅድስናችን ትግል ጣፋጭ እንጂ መራር ፍለጋ ያልሆነው። ለዓለም መብለጭለጮች ባሮች መሆናችን በክርስቶስ ተሰብሯል። ሥሉስ የሆነው አምላክ በእምነት ታላቅ መዝገባችን ሆኗል። ደስተኞች ሆነን ለመታዘዝ ነፃ ነን።
የቅድስናችን ትግል ጣፋጭ እንጂ መራር ፍለጋ ። ለዓለም መብለጭለጮች ባሮች መሆናችን በክርስቶስ ተሰብሯል።
ነገር ግን ስለቅድስናችን ያለን ሩጫ እንድናጉረመርም ካደረገን በትክክል እያደረግነው አይደለም። ምክንያቱም የዚህ ዓለም ማታለል ከብቦን የቅድስናን ምንነት ግራ እንዲገባን ስላደረገን ነው። ወይንም ደግሞ ዓለም ከወደፊት ደስታ ይልቅ አሁኑኑ በኃጢያት መርካት እንደሚሻል እንድናምን ስላምትፈልግ ነው።
ስጋችን ደካማ ስለሆነ ኃጢያታችንን እየተናዘዝን የወንጌልን ጸጋ በሕይወታችን ላይ እንለማመዳለን (1 ዮሐንስ 1፡8-10)። ነገር ግን በምንወድቅበት ጊዜ እንኳ ዳግም የተወለዱ የእግዚአብሔር ልጆች ተነስተው ከዚህ ዓለም ማታለል አሻግረው ይመለከቱና የእግዚአብሔር ትዕዛዛት ከማር ይልቅ ለዳነው ምላሳቸው ጣፋጭ እንደሆነ እና ደስታ ለዘላለም ወደሚፈስበት ቤታቸው (መዝሙር 16፡11) እየወሰዳቸው እንደሆነ በማመን በእምነት ይራመዳሉ።
ደስታ አሳሳቢ ጉዳይ እንደሆነ ፓስተር ጆን ይጽፋል። “እጃችንን እየቆረጥን የምንፋለምበት አይነት አሳሳቢ ጉዳይ" (ማቴዎስ 5፡30) ያለንን ሁሉ የሚያሸጠን (ማቴዎስ 13፡44) ደግሞም በቀራንዮ ከኢየሱስ ጋር መስቀል ተሸክመን የምንሄድበት ነው(ማቴዎስ 10፡38-39)። ጠባሳዎች አሉት። የደስታን መዝሙሮችን ከእንባ ጋር ይዘምራል። ያለፉትን ጨለማ ጊዜያት ያስታውሳል። የበለጠም እንደሚመጣ ያውቃል። ወደ መንግስተ ሰማይ የሚወስደው መንገድ በእርግጥ አስቸጋሪ መንገድ ነው ግን ደስታ የሌለበት አይደለም።
Originally Posted at DesiringGod.org, Translated by Joshua Terefe