Tuesday, 22 October 2024

ወደ እግዚአብሔር መቅረብ (ክፍል 1)

Posted On %AM, %10 %041 %2016 %03:%Oct Written by

ወደ አንድ ሰው ቤት ወይንም የሥራ ቦታ ሄዳችሁ ያንን ሰው ቀርቦ መገኛኘት አስጨንቋችሁ ያውቃል? የምትገናኙበት ጊዜ በደረሰ ጊዜ ልትነግሩት ያሰባችሁት ሁሉ ስትለማመዱት የቆያችሁት ነገር ሁሉ ከጭንቅላታችሁ ውስጥ በንኖ ጠፍቶ መናገር እንደምትችሉ ሁላ እርግጠኛ ላትሆኑ ትችላላቸሁ።

እንደ ሰውየው እና እንደሁኔታው ዓይነት ደግሞ እጅግ ከእነእርሱ ያነሳችሁ አሊያም ጊዜአቸውን እያባከናችሁ እንደሆነ ሊሰማችሁ ይችላል። በመጀመሪያችሁ በእዚህ ቅርርብ እነእርሱን መማረክ እንዳለባችሁና እናንተን የሚያዩበት መነፅር ደግሞ በእዚህ የመጀመሪያ ግንኙነታችሁ ላይ ሊወሰን እንደሚችል ሊሰማችሁ ይችላል። እንደዚህ በሚሆንበት ጊዜ ከእናንተ ጋር ወዳጅነት ሊመሠርቱ በሚመጡበት ጊዜ ልታቀርቡላቸው ከምትችሉት ነገር ይልቅ ስለሰራችኋቸው ጥፋቶች እንድታስቡ ያደርጋችኋል።

መልካም ወዳጅነት ካለን ሰው ጋር ግን ሲሆን ለመቅረብ ብዙም አንቸገርም።ጥሩ ስሜት በማይሰሙን አሰቀያሚ ቀኖቻችን ሳይቀር ከእነእርሱ ጋር ምቾት ይሰማናል። በቀላሉ ወደ እነእርሱ ቀርበን በልባችን ውስጥ ስላለው ነገር በነፃነት ልናናግራቸው እንችላለን።

እዚህ ምድር ላይ ያሉ ሰዎችን ቀርበን የምንገናኝበትን መንገድ በሰማይ ያለውን አምላካችንን ቀርበን የምንገናኝበት መንገድ ጋር ሊዛመድብን ይችላል። ሩቅ እንደሚኖር ባዳ ለእኛ ጊዜ የሌለው ጉዳዮቻችንን ከመስማት ይልቅ በሌላ ሥራ እንደተጠመደ አድርገን ምናስበው ከሆነ ወደ እርሱ ስንቀርብ በታላቅ ጥንቃቄ ይሆናል አልያም ወደ እርሱ ላንቀርብ እንችላለን። የልባችንን ሊሰማ ፍቃደኛ ልብ እንዳለው እና ጓደኛችን አድርገን ብናየው በተለየ መልኩ ወደ እርሱ እንቀርባለን።

እግዚአብሔር ወደ እርሱ እንድንቀርብ ይፈልጋል። ወደ እኛ መቅረብ ይችል ዘንድ ወደ እርሱ እንድንቀርብ ይፈልጋል። የመጀመሪያውን እርምጃ እንድንወስድ እየጠበቀን ነው። ምን እንደተከሰተ አስቀድሞ ስለሚያውቅ ልንነግረው ስላለው ነገር አይፈራም። ይሁን እንጂ ቀድመን መንፈስ ቅዱስ ጋር ስለሆነ የምንደርሰው ከእርሱ ጋር ምቾት እንዲሰማን ይፈልጋል።

እግዚአብሔር ፍቅር እንደሆነ መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል። ወደ እግዚአብሔርም የምንቀርብበት መንገድ ደግሞ ስለዚህ እውነት ባለን መረዳት ላይ የተመሠረተ ነው። ወደ ፍቅር እንዴት መቅረብ እንችላለን? እንዲህ መሆኑ ወደ እርሱ እንድትቀርቡ ያደርጋችኋል ወይንስ ርቃችሁ እንድትቆሙ? የዚህ ሁሉ መሠረት ፍቅር ለእኛ ምን እንደሚመስል እና ስለ ፍቅር ያለን መረዳት ነው። 

1 ቆሮንቶስ 13 "ፍቅር ታጋሽ ነው" ይላል። እኛ ከምንታገሠው በላይ አብልጦ ይታገሠናል። ፍቅር ቸርነትን ያደርጋል፤ ክፉ አይደለም! ጨቋኝ አይደለም! በኃጢያታችን እንኳ እያለን ለእኛ ቸር ነው። (ሮሜ 5፡8 “ነገር ግን ገና ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶአልና እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያስረዳል”።) ይሄ የእርሱ ቸርነት ነው። ፍቅር አይቀናም። ቅንአት እኛ የምንፈልገው ነገር ያላቸውን ሁሉ እንድንጠላ ያደርጋል። እግዚአብሔር ግን መሻታችንን ስናገኝ ደስ ይለዋል። ሃሳቡ የልባችንን መሻት መስጠት ነው። ምዕራፉ ፍቅር ምን እንደሆነ ሊያስረዳን ይቀጥላል። ፍቅሩ ያለ ገደብ ይወድደናል። 

ስለዚህ ንጹህ ፍቅር ወደሆነው ወደ እግዚአብሔር ስንቀርብ መጽሐፍ ቅዱስ የሚከተሉትን ቀላል መመሪያዎች ይሰጠናል።

ዕብራውያን 4፡12-16

“የእግዚአብሔር ቃል ሕያው ነውና፥ የሚሠራም፥ ሁለትም አፍ ካለው ሰይፍ ሁሉ ይልቅ የተሳለ ነው፥ ነፍስንና መንፈስንም ጅማትንና ቅልጥምንም እስኪለይ ድረስ ይወጋል፥ የልብንም ስሜትና አሳብ ይመረምራል፤  እኛን በሚቆጣጠር በእርሱ ዓይኖቹ ፊት ሁሉ ነገር የተራቆተና የተገለጠ ነው እንጂ፥ በእርሱ ፊት የተሰወረ ፍጥረት የለም። እንግዲህ በሰማያት ያለፈ ትልቅ ሊቀ ካህናት የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ስላለን፥ ጸንተን ሃይማኖታችንን እንጠብቅ። ከኃጢአት በቀር በነገር ሁሉ እንደ እኛ የተፈተነ ነው እንጂ፥ በድካማችን ሊራራልን የማይችል ሊቀ ካህናት የለንም። እንግዲህ ምሕረትን እንድንቀበል በሚያስፈልገንም ጊዜ የሚረዳንን ጸጋ እንድናገኝ ወደ ጸጋው ዙፋን በእምነት እንቅረብ”።

በመጀመሪያ ይህ ክፍል ስለ እግዚአብሔር ቃል ይናገራል። የሀሳባችን እነዲሁም የልባችን መርማሪ እንደሆነ ይናገራል። በመቀጠልም ወደ ቅዱስተ ቅዱሳኑ ሊገባ ስለተቻለው የብሉዩን ኪዳን ሊቀ ካህን ስለተካው የአዲሱ ኪዳን ሊቀ ካህን ደግሞ ይናገራል። ኢየሱስ በመስቀል ላይ ሲሞት ሁላችንም ወደዚያ ቅዱስ ስፍራ መግባት እንችል ዘንድ መጋረጃው እንደተቀደደ ይነግረናል።

ኢየሱስ በነገር ሁሉ የደረሱብንን ነገሮች ይረዳናል። ስላለብን ውጊያ ጥልቅ የሆነ መረዳት አለው። ሊማልድልንም ከአባቱ ጋር ተቀምጧል። ወደ ዙፋኑ በድፍረት እንድንቀርብ እየጋበዘን ነው። አትፍሩ እያለን ነው። ምን እንደሆነ አስቀድሜ አውቃለሁ! ቃሉን ስታነቡ ስላላችሁበት ሁኔታ እውነቱን በልባችሁ በተረዳችሁ ጊዜ ስላስፈለጋችሁ እርዳታ የሚሆን ጸጋ እና ምህረት ልሰጣችሁ በእጄ አለኝ። ሲፈርድባችሁ የነበረው እርሱ እንጂ እኔ አይደለሁም። ወደ ፍርድ ዙፋን ሳይሆን ወደሚረዳችሁ የጸጋ ዙፋን ነው እየቀረባችሁ ያለው። 

“ቃሉን የሚሰማ የማያደርገውም ቢኖር የተፈጥሮ ፊቱን በመስተዋት የሚያይን ሰው ይመስላል፤ ራሱን አይቶ ይሄዳልና፥ ወዲያውም እንደ ምን እንደ ሆነ ይረሳል። ነገር ግን ነጻ የሚያወጣውን ፍጹሙን ሕግ ተመልክቶ የሚጸናበት፥ ሥራንም የሚሠራ እንጂ ሰምቶ የሚረሳ ያልሆነው፥ በሥራው የተባረከ ይሆናል” (ያዕቆብ 1፡23-25)።

እንደ ክርስቲያኖች በምንኖረው ነሮ ለሚኖረን ውጊያ የእግዚሐብሔር ቃል ወሳኝ መሣሪያ ነው። የልባችንን ድካም እና ስህተቶች እየገለጠ በአሸናፊዎች ወገን እንድንሆን ያደርገናል። የእግዚአብሔር ቃል በሚገልጥልን ነገሮች ምን እንደምናደርግ ግን ምርጫው የእኛ ነው። እንደዚያ መልኩን አይቶ እንደሚሄደው ደግሞም እንደማይቀየረው ሰው መሆን ሊያምረን ይችል ይሆናል። ነገር ግን በተለወጥን ጊዜ ነፃነት እና በረከትን እናገኛለን።

ስለ እግዚአብሔር ቃል አላማ ያለን መረዳት ልክ ያልሆነ  ከሆነ እንዲቀይረን ስፍራ ላንሰጠው እንችላለን። የተሳለ ስለሆነ ሊወጋን ይችላል። ነገር ግን በልባችን ውስጥ የተጋለጠውን ኃጢያት ማሸነፍ እንችል ዘንድ ጸጋውን እና ምህረቱን እንዲያሳየን ከእርሱ ሳይሆን ወደእርሱ የመሸሽ መብት አለን።

ኢየሱስ “የመቤዣ ዋጋችሁን ከፍያለሁ። በመስቀል ላይ ስሞትላችሁ ዋስ ሆኛችኋለሁ ስለዚህ ወደ እኔ ኑ! ስለ ትህትናችሁ ማበረታቻ ጸጋን ልሰጣችሁ እፈልጋለሁ። በእፍረታችሁ ፈንታ ምህረትን ልሰጣችሁ እፈልጋለሁ።” እያለን እንደሆነ ልናስብ እንችላለን።

ወደ እግዚአብሔር ስንቀርብ እና ወደ መገኘቱ አንድ እርምጃን ስንወስድ ትቶን ወደኋላ አያፈገፍግም ደግሞም እንዳንመጣ አይከለክለንም። ይልቁንም ወደ እኛ ይጠጋል የበለጠ ወደ እኛ ይቀርባል። እጆቹን ዘርግቶ ወደ ምቹው እቅፉ ይቀበለናል። ትዕቢተኛን ይቃወማል ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል። ወደ እግዚአብሔር ስንቀርብ “ጌታ ሆይ ታስፈልገኛለህ። ይህንን በእራሴ ማድረግ አልችልም” እያልን ነው። ወደ እርሱ ስንቀርብ ትሑታን እየሆንን ነው። የዚህን ጊዜ በፍቅሩ ይዳስሰናል። 

ወደ እግዚአብሔር መቅረብ (ክፍል 2)

Translated by Joshua Terefe


 

Last modified on %PM, %11 %891 %2017 %23:%Apr
Michelle Zombos

Born in Auckland, New Zealand to migrant parents from Western Samoa and Australia/Greece, Michelle declared at the age of six that one day she would be a “missionary” to Ethiopia. After giving her life to Jesus as a 19-year-old mother and wife, she started to serve in ministry in South Auckland’s urban community. After having her five children and graduating from Bible College, she eventually came to Ethiopia with her family where she has served a local Ethiopian Evangelical Mekane Yesus Church in Debre Zeit and Addis Ababa. She is passionate about the word of God and sharing it with those who long to connect with their Creator.

aheartforethiopia.blogspot.com/

ክርስቲያን ተማሪዎች በተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ እንዲማሩ የሚያበረታ…

ትምህርት ሚኒስቴር (የሃገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ) ባሳለፍነው አርብ መስከረም 24 ወደ መንግስት ዩኒቨርሲቲዎች (ከፍተኛ የትምህርት ተቋማ...

Naol Befkadu - avatar Naol Befkadu

ጨርሰው ያንብቡ

እግዚአብሔር እኔ ምን እንደሆንኩ ያስባል?

ሁላችንም ማን እንደሆንን ማወቅ እንፈልጋለን። እራሳችንን ፈልገን ለማግኘት እንጥራለን። ብዙዎቻችን የስብዕና ፈተናዎችን እና ሌላም ግምገማዎችን ወስደናል።  ይ...

Jonathan Parnell - avatar Jonathan Parnell

ጨርሰው ያንብቡ

 

The views and opinions expressed on Daily Injera are solely those of the original authors and our contributors. These views and opinions do not necessarily represent Daily Injera or our Staff.

Newsletter

Subscribe to our newsletter. Don’t miss any article, devotionals or wallpapers.

We do not spam!

You're automatically subscribed to bi-weekly articles and daily devotionals. You can customize your subscription settings here.