Tuesday, 19 March 2024

ክርስቶስ በጣቱ ምን ጻፈ?

Posted On %AM, %22 %963 %2017 %01:%Jan Written by

ይህን የመጽሀፍ ቅዱስ ታሪክ በማነብበት ጊዜ ሁሉ እጅግ መደነቄ የማይቀር ነው። ምናልባትም በገጠራማዋ ገሊላ ይልቁንም በዚች የወይራ ዛፎች ኮረብታ በምትሆን ደብረ ዘይት መንደር ውስጥ የሆነው ሙግት መጪውን የሰው ልጅ እጣ ፈንታ አስቀድሞ የሚያመለክት በመሆኑ ይሆናል።

ውብ ማለዳ ነበር-በተራራማዋ የወይራ ዛፎች ኮረብታ ደብረ ዘይት። ክርስቶስ በዚች ኋላ ቀር መንደር ውስጥ በሚገኝ መቅደስ የሰንበት ትምህርቱን እያስተማረ ነበር።ህዝቡ ከዚህ “ድኩም” ሰው የሚወጡትን አስደናቂ ቃላት ሊሰሙ ታድመዋል። ይህ መቅደስ ከትምህርቱም ሌላ አመንዝራን፣ ከሳሽን እና አምላክ መሆኑና አለመሆኑ የሚፈተን ጎልማሳን አስተናግዶ ነበር። በዚህች ውብ ማለዳ በሆነው ትእይንት እኔን የምታመለክት- አመንዝራ የመኖሯን ያህል አምላክን በአካል የወከለ ኢየሱስ መኖሩን አምናለሁ።

ይህን ማመን በአፋችን እንደምናወራው ቀላል አይደለም። በዚያ ዘመን ኖረን ቢሆን ኖሮ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን ልናምን እስኪሳነን አሁን እንደምናወራለት ጀብደኛ አልነበረም(የሚራብ፣የሚደክም፣የሚያለቅስ፣የሚመታ በመጨረሻም የሚሰቀል “መሲህ” ሆኖ መምጣቱ አንዳንዴ በዘመኑ የነበሩ ወገኖቹን ለማሰናከል የታሰበ እስኪመስል ድረስ ኢየሱስን ተራ ሰው ያደርጉታል። ድካሙ እና “ሰው”ነቱ የአደባባይ ሲሆን፤ጥቂቶች የመሰከሩለት ከሞት የመነሳት ጀብዱው ግን እምነት በሚባል መንፈሳዊ መነጽር ብቻ ሊታይ የሚችል ድብቅ መሆኑ ከዘመኔዎቹ ጋር እልህ የተጋባ ያስመስለዋል።)

በዚያች ውብ የትምህርት ማለዳ በምንዝር የተያዘችው ሴት ልብሶቿ እስኪቀደዱ እየተጎተተች ስትገባ አዳራሹ ውስጥ የተፈጠረውን ዝምታ እና በፈተናቸው ከባድነት የተማመኑትን ፈሪሳዉያን ኩራት መሳል ሁለቱም ቀላል ነበሩ። በአጭሩ በምንዝር እጅከፍንጅ መያዟ ተገልጾ “አንተስ ምን ትላለህ?” ወደሚለው ጥያቄ ዞሩ። “ዉገሯት” ቢል የሀጢያተኞች ወዳጅ አድርጎ ራሱን የሚስለው ክርስቶስ በነሱ ዘንድ ያለውን ዋጋውን ሊያጣ ነው። “አትውገሯት” ቢል ከአይሁድ ብሎም ከ ሙሴ ህግ ሊፋረስ ነው። “አንተ ግን አምላክ ብትሆን ምን ትላለህ?” አይነት ነው ጥያቄው። ክርስቶስ ግን ዝቅ ብሎ በጣቶቹ ጻፈ። በወንጌላት እንደሰፈረልን ክርስቶስ የጻፈበት ብቸኛ ቦታ ነው- ታዲያ ምን ብሎ ይሆን የጻፈው?

ደጋግመው በነዘነዙት ጊዜ ይጽፍ የነበረውን አቋርጦ የመለሰላቸው መልስ ግን ለዚያች አመንዝራ ብቻ ሳይሆን በህግ በተከሰስን ጊዜ ለሁላችንም የተመለሰው መልስ ስለመሆኑ እርግጠኛ ነኝ። “ከእናንተ ሀጢያት የሌለበት አስቀድሞ በድንጋይ ይውገራት” አላቸው። ለእኔ ይህ የአዲስ ኪዳን ማስጀመሪያ መለከት ነው። በህግ እና በእግዚአብሔር መካከል ያለውን ልዩነት በግልጽ የሚያሳይ ስፍራ ነው።ህጉም፤ ሰጪው ክርስቶስም አመንዝራነት ሀጢያት መሆኑን አልካዱም። ዳሩ ህግ ለተላላፊው ቅጣትን ሲያሰፍር ክርስቶስ ግን ደካማነታችንን በማየቱ ምህረትን ይሰጣል። ከቅጣት ይልቅ ምህረት የበዳይን ልብ ያቀናል።

ክርስቶስ ግን ይህን ተናግሮ ከሳሾቿም፤ወጋሪዎቿም ሆነው የመጡት ሰዎች ማንም ባያያቸውም ቅሉ ሀጢያተኞች መሆናቸውን ነግሮ ካሳፈረላትም በኋላ በጣቶቹ ይጽፋል-ዝቅ ብሎ አቧራ የጠጣውን በጥርብ ድንጋይ የተሰራ የመቅደሱን ወለል በጣቶቹ እየጠረገ። ምን ብሎ ይሆን የጻፈው?... የሁሌም የአግራሞት ጥያቄዬ።

ምናልባት፤እንደው ምናልባት ለእነዚያ ግብዝ ህግ አዋቂዎች “አብሯት ያመነዘረውን ረስታችሁት ነው ወይስ ከእናንተ አንዱ ነው?” ይሆን ያላቸው????

Last modified on %PM, %28 %454 %2017 %12:%Jan
Wongel Alemayehu

Wongel is a banker residing in Addis Ababa. He is an author of a novel called "Ke'enkib sir". He attends at Gullele Meserete Kirstos Church.

www.facebook.com/wongel.alemayehu.3/

ደስታችሁ ያረፈው በክርስቶስ ጽድቅ ላይ ነው

እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር እንደሆነ መቶ በመቶ ብታምኑ ምን የሚሆን ይመስላችኋል? እንደተቀበላችሁ ብቻ ሳይሆን በክርስቶስ ማንነት እና ሥራ ምክንያት ሙሉ ለሙሉ...

David Mathis - avatar David Mathis

ጨርሰው ያንብቡ

ከፖርኖግራፊ ሱስ እንዴት መውጣት ይቻላል?

ከፖርኖግራፊ ሱስ መውጣት ይቻላል! ክፍል 3 - ከፖርኖግራፊ ሱስ እንዴት መውጣት ይቻላል? በዚህ ተከታታይ ፅሁፍ የመጀመሪያ ክፍል ላይ ‘ፖርኖግራፊ’ ሰዎችን...

Ermias Kiros - avatar Ermias Kiros

ጨርሰው ያንብቡ

 

The views and opinions expressed on Daily Injera are solely those of the original authors and our contributors. These views and opinions do not necessarily represent Daily Injera or our Staff.

Newsletter

Subscribe to our newsletter. Don’t miss any article, devotionals or wallpapers.

We do not spam!

You're automatically subscribed to bi-weekly articles and daily devotionals. You can customize your subscription settings here.