Tuesday, 22 October 2024

ፀሀይ ግባት እና ወጀብ

Posted On %AM, %04 %041 %2017 %03:%Feb Written by

እግዚአብሔር ለክብሩ የተከላቸው የጽድቅ ዛፎች እንዲባሉ ለጽዮን አልቃሾች አደርግላቸው ዘንድ፥ በአመድ ፋንታ አክሊልን፥ በልቅሶም ፋንታ የደስታን ዘይት፥ በኀዘንም መንፈስ ፋንታ የምስጋናን መጐናጸፊያ እሰጣቸው ዘንድ ልኮኛል። ” (ኢሳይያስ 61፡3)

ላለፉት ሁለት ሳምንታት በሲድኒ አውስትራሊያ ነበር ያሳለፍኩት። ወቅቱ ፀደይ ስለነበር የአየሩ ሙቀት እየጨመረ ነው ፤ ቀኖቹም ረጅም እየሆኑ ነው። ፀሀይ በምትጠልቅበት ጊዜ ወጥቶ ለመንሸራሸር ደስ ይሚል አየር ነበር።

ሲድኒ ውስጥ ፀሀይ ስትጠልቅ በጣም የሚስብ እይታ ነው። እንዳስተዋልኩት ከሆነ ግን በጣም የሚያስደስት እይታ ያለው ሰማዩ ጥርት ባለባቸው ቀኖች ላይ አይደለም። ነገር ግን ሰማዩ በጨፈገገበት እና በደመና በተሞላባቸው ቀኖች ከምን ጊዜውም በላይ ያማሩ የፀሀይ ግባት እይታዎች ይኖራሉ። ደመናዎቹ ከፀሀይ የሚመጡትን የተለያዩ ቀለማት ያንፀባርቁና የእግዚአብሔርን ክብር በግልጽ ታዩታላችሁ። ሰዎች በሚያዩት ድንቅ ውበት ስለሚማረኩ ፎቶዎች እያነሱ በማሕበራዊ ድህረ ገጾች ላይ ያወጧቸዋል።

በህይወታችንም ብዙ ጊዜ ነገሮች እንዳቀድናቸው የማይሄዱባቸው ቀኖች ላይ ወይንም እንዳናረጋቸው የተገቡ ነገሮችን በማድረጋችን ምክንያት ደመናማ ቀኖችን አሊያም ደመናማ እና በወጀብ የተሞሉ ውብ ልንላቸው የማንችላቸው ወቅቶች በህይወታችን ውስጥ ልናይ እንችላለን። በወጀቡ ውስጥ የምናያቸው ደመናዎች ቀኑን ሙሉ ከሚያበራው ፤ ፈጽሞም ከማይተወን ወይንም ከማይጥለን የዓለም ብርሃን የሚጋርዱን ነገሮች ናቸው።

ፀሀይ ሁል ጊዜ በሰማይ ላይ እንዳበራች ነው። አይሮፕላን ላይ ተሳፍራችሁ የምታውቁ ከሆነ ደግሞ አንዴ ከደመና በላይ ከፍ ስትሉ የምታዩት ነገር ፀሀይ ብርሃኗን እየሰጠች እና ውብ ብርሃኗን ከደመናው በላይ እያንፀባረቀችው እንዳለ ነው። በደመና ውስጥ ሰንጥቆ ወጥቶ ልናየው ባንችልም ፀሀይ ግን ብርሃን መስጠቷን መቼም አታቋርጥም።


በህይወታችንም ብዙ ጊዜ ነገሮች እንዳቀድናቸው የማይሄዱባቸው ቀኖች ላይ ወይንም እንዳናረጋቸው የተገቡ ነገሮችን በማድረጋችን ምክንያት ደመናማ ቀኖችን አሊያም ደመናማ እና በወጀብ የተሞሉ ውብ ልንላቸው የማንችላቸው ወቅቶች በህይወታችን ውስጥ ልናይ እንችላለን። በወጀቡ ውስጥ የምናያቸው ደመናዎች ቀኑን ሙሉ ከሚያበራው ፤ ፈጽሞም ከማይተወን ወይንም ከማይጥለን የዓለም ብርሃን የሚጋርዱን ነገሮች ናቸው።


በህይወታችሁ ላይ ያንዣበበው ደመና እግዚአብሔር እንደሌለ ወይንም እንደተዋችሁ ማሰብ እንድትጀምሩ እድርጓችሁ ሊሆን ይችላል። ነገር ግን እሱ እንደማይተዋችሁ ቃል ገብቷል ይዋሽ ዘንድ ደግሞ አይችልም። ነገር ግን በህይወታችሁ ላይ የድንቅ ሥራውን ምስል ለማስቀመጥ እየሠራ ነው። በህይወታችሁ ውስጥ ያለውን ደመና ሰንጥቆ የወጣውን የብርሃኑን ነፀብራቅ ሰዎች ባዩ ጊዜ ይህንን ውበት በእናንተ ውስጥ ያመጣው እግዚአብሔር እንደሆነ ያውቃሉ።

ለህይወታችሁ ውበትን በመስጠት እግዚአብሔር ሰዎችን ወደ እውነተኛው ብርሃን ወደ ኢየሱስ ለመማረክ ይጠቀምባቸዋልና ወጀቦቹን አትፍሯቸው ከደመናዎቻችሁም አትደበቁ።

 

Translated by Joshua Terefe


 

Last modified on %AM, %04 %976 %2017 %01:%Feb
Michelle Zombos

Born in Auckland, New Zealand to migrant parents from Western Samoa and Australia/Greece, Michelle declared at the age of six that one day she would be a “missionary” to Ethiopia. After giving her life to Jesus as a 19-year-old mother and wife, she started to serve in ministry in South Auckland’s urban community. After having her five children and graduating from Bible College, she eventually came to Ethiopia with her family where she has served a local Ethiopian Evangelical Mekane Yesus Church in Debre Zeit and Addis Ababa. She is passionate about the word of God and sharing it with those who long to connect with their Creator.

aheartforethiopia.blogspot.com/

አስታውሱ ፤ ይወድዳችኋል

“እናንተ ግን፥ ወዳጆች ሆይ፥ ከሁሉ ይልቅ በተቀደሰ ሃይማኖታችሁ ራሳችሁን ለማነጽ እየተጋችሁ በመንፈስ ቅዱስም እየጸለያችሁ፥ ወደ ዘላለም ሕይወት የሚወስደውን ...

Joseph Tenney - avatar Joseph Tenney

ጨርሰው ያንብቡ

ሃሳባችሁን እንደ ውቅያኖስ ሰፊ በሆነው በእግዚአብሔር ሉአላዊነት…

አንዳንድ ጊዜ ሃሳባችንን እንደ ውቅያኖስ ሰፊ በሆነው በእግዚአብሔር ሉአላዊነት ውስጥ ልንጨምር ያስፈልገናል። ወደ ውስጥ በሰመጥን ቁጥር ክብደቱ ሊሰማን ይገባል...

John Piper - avatar John Piper

ጨርሰው ያንብቡ

 

The views and opinions expressed on Daily Injera are solely those of the original authors and our contributors. These views and opinions do not necessarily represent Daily Injera or our Staff.

Newsletter

Subscribe to our newsletter. Don’t miss any article, devotionals or wallpapers.

We do not spam!

You're automatically subscribed to bi-weekly articles and daily devotionals. You can customize your subscription settings here.