Saturday, 04 May 2024

በህይወቴ ላይ የእግዚአብሔር ፍቃድ ምንድን ነው? Featured

Posted On %AM, %11 %041 %2016 %03:%Oct Written by

የዚህን መልስ ማወቅ ሁላችንም እንፈልጋለን አይደል? ከዚህ በላይ ውጥረትን ሊፈጥር የሚችል ርዕስ ሊኖር ይችላል? ስለፈጠረን ፣ ደግሞም በሕይወት እያቆየን ስላለው ፣ ሊያድነን ልጁን ስለሰጠን ስለ ስለ ሉአላዊው እግዚአብሔር እያወራን ነው። በሰጠን እንፋሎት በሆነች በዚህች ሕይወት ውስጥ ምን እንድናርግለት ይፈልጋል? 

ተከተሉኝ (Follow Me) በሚለው መጽሐፉ ፕላት የእግዚአብሔርን ፍቃድ የመፈለጋችን ስር መሠረቱ ምን እንደሆነ ይናገራል። እጣ መጣል ቢሆን ወይንም እንደ ኤሊያስ ዝግተኛዋን ትንሽ ድምጽ መስማት አሊያም በሩ በፊታችን አውቆ እንዲከፈቱ መጠበቅ አይነት ወዳሉ ብዙ መንገዶችን ተስበናል። ነገር ግን ፕላት ይህን ያህል ከባድ ነው? ይለናል።

እግዚአብሔር ልጁን የላከው እርሱ በሰማይ ቁጭ ብሎ “አይ እንደሱ አይደለም. . . አሁን ልክ ነህ . . . አሁን ልክ ነው” ሊለን ባይሆንስ? የእግዚአብሔርን ፍቃድ በዚህ መልኩ መፈለግ ሙሉ በሙሉ የክርስቶስ ደቀመዝሙር የሚለውን ሀሳብ የሳተ ቢሆንስ? (ገጽ 127-128)

ክርስቲያናዊ ደቀ መዝሙርነት አላመው ፍቃዳችንን መቀየር ነው። አማኞች በክርስቶስ አዲስ ሲሆኑ የሆነው ይህ ነው። “እንደ ኢየሱስ ተከታዮች ሕይወታችን በሕይወቱ ውስጥ የተካተተ ነው። መንገዳችንም ለፍቃዱ ሙሉ በሙሉ የተገዛ ነው” (ገጽ 128)። በክርስቶስ መሆን ማለት “ከእንግዲህ ወዲህ ስለ እኛ ለሞተውና ለተነሣው እንጂ ወደ ፊት ለራሳችን አንኖርም” (2 ቆሮንቶስ 5፡15) ማለት ነው።


እግዚአብሔር ልጁን የላከው እርሱ በሰማይ ቁጭ ብሎ “አይ እንደሱ አይደለም. . . አሁን ልክ ነህ . . . አሁን ልክ ነው” ሊለን ባይሆንስ? የእግዚአብሔርን ፍቃድ በዚህ መልኩ መፈለግ ሙሉ በሙሉ የክርስቶስ ደቀመዝሙር የሚለውን ሀሳብ የሳተ ቢሆንስ?


እንደዚህ ከሆነ ታዲያ እጆቻችንን አጣምረን በተቆጣ ፊት ወደ እግዚአብሔር መመልከት ትንሽ እንግዳ ነገር አይሆንም? እኛ የእራሳችን አይደለንም ነገር ግን “ማንኛውም ነገር ይሁን ጌታ ሆይ ከእነዚህ ምርጫዎች ውጪ ማንኛውም ነገር ይሁን" እንላለንን? ከክርስቶስ ጋር ስላለን ሕብረት በማስተዋል እየኖርን ከሆነ “ወደምትመራኝ ሁሉ እሄዳለሁ ከእኔ የምትጠይቀውን ሁሉ እሰጣለሁ” ከማለት የተለየ ነገር ለእግዚአብሔር ልንናገር እንችላለን? ፕላት ሲጽፍ “በክርስቶስ ውስጥ የእራሳችንን ሕይወት አጥተነዋል፣ በደስታ ፍቃዳችንን ለእርሱ እናሰገዛለን። ይህ በምንጠመቅበት ጊዜ የታወጀ እና የተደነገገ ደቀ መዝሙር የመሆን ትርጉም ነው” (ገጽ 130)።

ስለዚህ ለሕይወታችን የእግዚአብሔርን ፍቃድ ስንፈልግ የመጀመሪያው ነገር ፍቃዳችን በክርስቶስ ውስጥ እንደ አዲስ እንደተመሠረተ ማወቅ ነው። በዚህ ሴሚስተር ምን ማድረግ እንዳለብን ወይንም ከቀረቡልን የሥራ ምርጫዎች ውስጥ አንዱን መምረጥ ወይንም ሀገር ስለመቀየር ቢሆን በእግዚአብሔር ሀሳብ ውስጥ ምንም አቋራጭ መንገድ የለም። ፕላት ይሄ የእግዚአብሔር ሀሳብ እንዳልሆነ ያስታውሰናል።


ስለዚህ ለሕይወታችን የእግዚአብሔርን ፍቃድ ስንፈልግ የመጀመሪያው ነገር ፍቃዳችን በክርስቶስ ውስጥ እንደ አዲስ እንደተመሠረተ ማወቅ ነው።


እግዚአብሔር የሚያሳስበው እናንተን ከነጥብ ሀ ወደ ለ ፈጣን ፣ ቀላል ፣ የማያስቸግር በጣም ግልጽ በሆነው መንገድ ማድረስ አይደለም። ነገር ግን የሚያሳስበው እኔ እና እናንተ በእርሱ ሙሉ በሙሉ በታመንን ጊዜ እርሱን በጥልቅ ማወቃችን ነው። (ገጽ 131)

አያችሁ የተጠራነው ከኢየሱስ ጋር ሕብረት እንድናደርግ ነው። የተጠራነው ወደ እራሱ አንጂ ወደ መመሪያዎች አይደለም። ፕላት ሲጽፍ “ስለዚህ የኢየሱስ ደቀ መዝሙርነት አላማው ‘ለሕይወቴ የእግዚአብሔር አላማ ምንድን ነው?’ የሚለውን መመለስ ሳይሆን ቀን በቀን በእያንዳንዷ አፍታ በእግዚአብሔር ፍቃድ ውስጥ መራመድ ነው” (ገጽ 133)። ዋናው ነገር ከኢየሱስ ጋር መራመድ ነው። ከእርሱ ጋር የምንራመድ ከሆነ ሕይወታችን በእርሱ ሕይወት የተዋጠ ከሆነ በትክክለኛው መንገድ እንጓዛለን።


እግዚአብሔር የሚያሳስበው እናንተን ከነጥብ ሀ ወደ ለ ፈጣን ፣ ቀላል ፣ የማያስቸግር በጣም ግልጽ በሆነው መንገድ ማድረስ አይደለም። ነገር ግን የሚያሳስበው እኔ እና እናንተ በእርሱ ሙሉ በሙሉ በታመንን ጊዜ እርሱን በጥልቅ ማወቃችን ነው። 


 

Originally Posted at DesiringGod.org, Translated by Joshua Terefe


 

Last modified on %PM, %10 %861 %2016 %22:%Dec
Jonathan Parnell

Jonathan Parnell is the lead pastor of Cities Church in Minneapolis/St. Paul, where he lives with his wife, Melissa, and their five children. He is co-editor of Designed for Joy: How the Gospel Impacts Men and Women, Identity and Practice.

https://twitter.com/jonathanparnell

እኛም ደግሞ የበደሉንን ይቅር እንደምንል በደላችንን ይቅር በለን

ማቴዎስ 6፡14-15 “ለሰዎች ኃጢአታቸውን ይቅር ብትሉ፥ የሰማዩ አባታችሁ እናንተን ደግሞ ይቅር ይላችኋልና፤ ለሰዎች ግን ኃጢአታቸውን ይቅር ባትሉ፥ አባታችሁም...

John Piper - avatar John Piper

ጨርሰው ያንብቡ

የእግዚአብሔር ፍቅር ቀድሞ እና አሁን

ነገር ግን ገና ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶአልና እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያስረዳል (ሮሜ 5፡8)።

John Piper - avatar John Piper

ጨርሰው ያንብቡ

 

The views and opinions expressed on Daily Injera are solely those of the original authors and our contributors. These views and opinions do not necessarily represent Daily Injera or our Staff.

Newsletter

Subscribe to our newsletter. Don’t miss any article, devotionals or wallpapers.

We do not spam!

You're automatically subscribed to bi-weekly articles and daily devotionals. You can customize your subscription settings here.